Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947

ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ በማህበር በመደራጀት ከተገኘዉ ይዞታ ጋር የተያያዘ ሲሆን አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት  ክስ በ03/08/1990 ዓ/ም ተመዝግቦ በፀደቀዉ የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የተደራጀ ታቦር የመኖሪያ ቤቶች ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል በመሆን ተደራጅተዉ ማኅበሩ በሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ካገኘዉ ጠቅላላ ይዞታ ላይ መጠኑ 203.67 ካሬ ሜትር የሆነዉን የክርክሩን ይዞታ   በድርሻ እንደሰጣቸዉና የዚሁ ይዞታ ሕጋዊ ባለመብት ስለመሆናቸዉም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 281839 በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤትና በኮልፌ  ቀራኒዮ ክለ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት ላይ ክስ አቅርበዉ መብታቸዉ ተረጋግጦ ዉሳኔ እንዲያገኝ የሚል ነው፡መልካም ንባብ…

Previous Article ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243
Next Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Print
6209

Documents to download

  • 259947(.pdf, 828.26 KB) - 754 download(s)

«July 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
293012345
6789101112
13141516171819
20212223242526
272829303112
3456789

ፍርድ ቤቱ እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት...

2949
የፈደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንሰቲትዩት በቴክኖሎጂ ዘርፍ አብሮ ለመስራት የሚያስችልላቸውን የመግባቢያ ስምምነት በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ መጋቢት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ተፈራረሙ።

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የአስተዳደር ሠራተኞች ረቂቅ ደንብ...

2768
ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀረበው የፌደራል ፍርድ ቤቶች የአስተዳደር ሠራተኞች ረቂቅ ደንብ ይዘት ላይ በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሥራ ኃላፊዎች አማካኝነት ለም/ቤቱ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ እና ለሰው ሐብት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት መጋቢት 11 ቀን 2015 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ማብራሪያ ተሰጠ፡፡

ለፍትሕ ሥርዓቱ ውጤታማነት የዳኞች፣ የአቃቢያነ-ሕግ እና...

2931
የፍትሕ ሥርዓቱ ውጤታማነት እንዲረጋገጥ ዳኞች፣ አቃቢያነ-ሕግ እና ጠበቆች ሙያዊ ነጻነት ኖሮአቸው በፍትሕ ሥርዓቱ ሊሳተፉ እንደሚገባ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምሕረት ገለጹ፡፡

ለቋሚ ኮሚቴ አባላት በፌደራል ፍርድ ቤቶች አስተደደር...

2703
በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚፀድቅ በሚጠበቀው የፌደራል ፍርድ ቤቶች አስተዳደር ሠራተኞች ረቂቅ ደንብ ይዘት ላይ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ እና ለሰው ሐብት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና አባላት መጋቢት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ገለጻ ተደረገ፡፡
First5960616264666768Last