Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398

የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ ስድስት) ካርቶን የተለያዩ የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ከቻይና ተጓጉዘው ሞጆ ደረቅ ወደብ እስኪደርሱ ድረስ ጉድለትን ጭምሮ ለሚደረስ ማንኛውም ጉዳት በመድን ፖሊስ ቁጥር GU/34/2011/2019/00114 አጠቃላይ የመድህን ሽፋን የሰጣቸው ዕቃዎች ሞጆ ደረቅ ወደብ ደርሰው ከሳሽ ከመረከቡ በፊት ዕቃዎች ገበያ ላይ በመታየታቸው ፍተሻ ተደርጎ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት እንዲፈፀም ህዳር 15 ቀን 2012 ዓ.ም ከሳሽ አቤቱታ አቅርቦ የጉምሩክ ጽ/ቤት ተወካይ፤አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት እና የከሳሽ ማኅበር ተወካዮች በተገኙበት ህዳር 17 ቀን 2012 ዓ.ም ዕቃዎቹ የመጡበት ኮንቴነር ተከፍቶ ሲፈተሸ የዋጋ ግምታቸው ብር 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) የሆነ 171 እሽግ መጉደሉ ተረጋግጦ አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የጎደሉ ዕቃዎችን በዝርዝር በመያዝ ወደ መጋዘኑ ማስገባቱንና ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ አጓዡ ኃላፊነት ወስዶ የጉድለት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ስላልሰጠው የካሳ ክፍያ ጥያቄውን ማስተናገድ አልችልም ማለቱን ጠቅሶ ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ በገባው የማሪን ውል መሰረት የጎደሉ ዕቃዎች ዋጋ 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) ካሳ ማስጠንቀቂያ ከደረሰው ከግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ፤ ከወጪ እና ኪሳራ ጭምር እንዲከፍለው ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942
Next Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Print
1817
«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ አሰባሰብ...

2026

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ አሰባሰብ ስርዓቱን አዘምኗል፡፡ 

ፍርድ ቤቱ ማንኛውንም የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ በሚከፈለው ብር መጠን ሳይገድብ፣ ባለጉዳዮች ወደ ባንክ መሄድ እና ጥሬ ገንዘብ ማቅረብ ሳያስፈልጋቸው ክፍያ መፈፀም የሚችሉበት የአሰራር ማሻሻያ አድርጓል፡፡  በዚህ የክፍያ አፈጻጸም ማሻሻያ ስርዓት፡-

የ2014 አዲስ ዓመት ጅማሬን አስመልክቶ ከጠቅላይ ፍ/ቤት...

2275

ክቡራንና ክቡራት ዳኞች

ያጠናቀቅነው የ2013 ዓ.ም በፍርድ ቤታችን ጉልህ የሚባሉ የማሻሻያ ሥራዎች የተከናወኑበትና በዚህ ረገድ በቀጣይ ለሚመዘገቡ ስኬቶች መሠረት የተጣለበት ሆኖ የሚወሰድ ነው፡፡

ባሳለፍነው ዓመት ለፍርድ ቤቱ የማሻሻያ ሥራ መሠረታዊ ከሆኑት እና በፍርድ ቤቶች የዳኞችን እና ተቋማዊ ነጻነትን፣ ገለልተኝነትን እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል የተሻሻሉት የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ እና የፌደራል የዳኝነት አስተዳደር አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ፀድቀው ወደሥራ መግባታቸው ጉልህ ሥፍራ የሚሰጠው ነው፡፡

እነዚህን አዋጆች ተግባራዊ ለማድረግም በርካታ ደንቦችና መመሪያዎች እየተዘጋጁና እየጸደቁ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ ከእነዚህ መካከል የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ እና የዳኞች ሥነምግባር እና የዲሲፒሊን ሥነሥርዓት ደንብ የፀደቁ ሲሆኑ በቅርቡ ፀድቀው ወደትግበራ እንደሚገቡ ከሚጠበቁት መካከል የአስተዳደር ሰራተኞች መተዳደሪያ ደንብ እና የዳኞች የሥራ አፈጻጸም ምዘና መመሪያ ይጠቀሳሉ፡፡

በፍርድ ቤቱ ለፍትሃ ብሔር ገዳዮች ፍሰት አስተዳደር...

2068

በፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር አስተባባሪ ዳይሬክቶሬት በፍርድ ቤቱ የፍትሃ ብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመተግበር ምቹ አስቻይ ሁኔታ ያለ መሆኑን ባካሄደው የዳሰሳ ጥናት ማረጋገጡን ገለጸ::

First6061626365676869Last