Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
2655

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 485 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ አሰባሰብ...

2026

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ አሰባሰብ ስርዓቱን አዘምኗል፡፡ 

ፍርድ ቤቱ ማንኛውንም የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ በሚከፈለው ብር መጠን ሳይገድብ፣ ባለጉዳዮች ወደ ባንክ መሄድ እና ጥሬ ገንዘብ ማቅረብ ሳያስፈልጋቸው ክፍያ መፈፀም የሚችሉበት የአሰራር ማሻሻያ አድርጓል፡፡  በዚህ የክፍያ አፈጻጸም ማሻሻያ ስርዓት፡-

የ2014 አዲስ ዓመት ጅማሬን አስመልክቶ ከጠቅላይ ፍ/ቤት...

2275

ክቡራንና ክቡራት ዳኞች

ያጠናቀቅነው የ2013 ዓ.ም በፍርድ ቤታችን ጉልህ የሚባሉ የማሻሻያ ሥራዎች የተከናወኑበትና በዚህ ረገድ በቀጣይ ለሚመዘገቡ ስኬቶች መሠረት የተጣለበት ሆኖ የሚወሰድ ነው፡፡

ባሳለፍነው ዓመት ለፍርድ ቤቱ የማሻሻያ ሥራ መሠረታዊ ከሆኑት እና በፍርድ ቤቶች የዳኞችን እና ተቋማዊ ነጻነትን፣ ገለልተኝነትን እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል የተሻሻሉት የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ እና የፌደራል የዳኝነት አስተዳደር አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ፀድቀው ወደሥራ መግባታቸው ጉልህ ሥፍራ የሚሰጠው ነው፡፡

እነዚህን አዋጆች ተግባራዊ ለማድረግም በርካታ ደንቦችና መመሪያዎች እየተዘጋጁና እየጸደቁ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ ከእነዚህ መካከል የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ እና የዳኞች ሥነምግባር እና የዲሲፒሊን ሥነሥርዓት ደንብ የፀደቁ ሲሆኑ በቅርቡ ፀድቀው ወደትግበራ እንደሚገቡ ከሚጠበቁት መካከል የአስተዳደር ሰራተኞች መተዳደሪያ ደንብ እና የዳኞች የሥራ አፈጻጸም ምዘና መመሪያ ይጠቀሳሉ፡፡

በፍርድ ቤቱ ለፍትሃ ብሔር ገዳዮች ፍሰት አስተዳደር...

2068

በፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር አስተባባሪ ዳይሬክቶሬት በፍርድ ቤቱ የፍትሃ ብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመተግበር ምቹ አስቻይ ሁኔታ ያለ መሆኑን ባካሄደው የዳሰሳ ጥናት ማረጋገጡን ገለጸ::

First6061626365676869Last