Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395 ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594 Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230 Print 7349 Documents to download 266395(.pdf, 849.74 KB) - 971 download(s)
በፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ነጻነት፣ ተጠያቂነትና... በፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ነጻነት፣ ተጠያቂነትና... Monday, March 13, 2023 2827 በፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ነጻነት፣ ተጠያቂነትና የሕግ ማዕቀፎች ዙሪያ ከሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ እና ከሰው ሐብት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም የምክክር መድረክ ተካሔደ፡፡ Read more
የሰበር ሂደት በሚመራበት ረቂቅ የሥነሥርዓት መመሪያ ላይ... የሰበር ሂደት በሚመራበት ረቂቅ የሥነሥርዓት መመሪያ ላይ... Friday, March 10, 2023 2936 በረቂቅ ደረጃ በሚገኘው የሰበር ረቂቅ የሥነሥርዓት መመሪያ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል ተካሔደ፡፡ Read more
በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት... በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት... Thursday, March 9, 2023 2461 የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሴቶችን ተሳትፎና እኩልነት ለማረጋገጥ የሚረዱ የተለያዩ የፖሊሲ እርምጃዎችን እየወሰደ እንደሚገኝ የፍ/ቤቱ ም/ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡ Read more
የፍርድ ቤቱ ዳኞች የሰበር ሂደት በሚመራበት ረቂቅ... Monday, March 6, 2023 2698 የሰበር የዳኝነት አሰጣጥ ስርዓት ግልጽ፣ ቀልጣፋ፣ ተገማች እና ውጤታማ ለማድረግ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተዘጋጀ ረቂቅ የሰበር የሥነሥርዓት መመሪያ ረቂቅ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የፍርድ ቤቱ ዳኞች ውይይት አካሔዱ፡፡ Read more
10Mar2026 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Tuesday, March 10, 2026 Read more