Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398

የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ ስድስት) ካርቶን የተለያዩ የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ከቻይና ተጓጉዘው ሞጆ ደረቅ ወደብ እስኪደርሱ ድረስ ጉድለትን ጭምሮ ለሚደረስ ማንኛውም ጉዳት በመድን ፖሊስ ቁጥር GU/34/2011/2019/00114 አጠቃላይ የመድህን ሽፋን የሰጣቸው ዕቃዎች ሞጆ ደረቅ ወደብ ደርሰው ከሳሽ ከመረከቡ በፊት ዕቃዎች ገበያ ላይ በመታየታቸው ፍተሻ ተደርጎ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት እንዲፈፀም ህዳር 15 ቀን 2012 ዓ.ም ከሳሽ አቤቱታ አቅርቦ የጉምሩክ ጽ/ቤት ተወካይ፤አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት እና የከሳሽ ማኅበር ተወካዮች በተገኙበት ህዳር 17 ቀን 2012 ዓ.ም ዕቃዎቹ የመጡበት ኮንቴነር ተከፍቶ ሲፈተሸ የዋጋ ግምታቸው ብር 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) የሆነ 171 እሽግ መጉደሉ ተረጋግጦ አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የጎደሉ ዕቃዎችን በዝርዝር በመያዝ ወደ መጋዘኑ ማስገባቱንና ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ አጓዡ ኃላፊነት ወስዶ የጉድለት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ስላልሰጠው የካሳ ክፍያ ጥያቄውን ማስተናገድ አልችልም ማለቱን ጠቅሶ ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ በገባው የማሪን ውል መሰረት የጎደሉ ዕቃዎች ዋጋ 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) ካሳ ማስጠንቀቂያ ከደረሰው ከግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ፤ ከወጪ እና ኪሳራ ጭምር እንዲከፍለው ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942
Next Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Print
5633
«July 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
293012345
6789101112
13141516171819
20212223242526
272829303112
3456789

የፍርድ ቤቱ ዳኞች የሰበር ሂደት በሚመራበት ረቂቅ...

2803

የሰበር የዳኝነት አሰጣጥ ስርዓት ግልጽ፣ ቀልጣፋ፣ ተገማች እና ውጤታማ ለማድረግ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተዘጋጀ ረቂቅ የሰበር የሥነሥርዓት መመሪያ ረቂቅ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ የፍርድ ቤቱ ዳኞች ውይይት አካሔዱ፡፡

የወንጀል ህጉ ለህጻናት ትኩረት አለመስጠቱ ከህጻናት ጋር...

2850

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የተቋቋመዉ የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የካቲት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በሕጻናት ጉዳይ ላይ ለሚሰሩ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት፣ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዳኞችና ለሶሻል ወርክ ባለሙያዎች ባዘጋጀዉ የሥልጠና መድረክ ላይ ከህጻናት ጋር ተያያዥነት ላላቸዉ ወንጀሎች መበራከት ዋነኛ መንስኤዉ የወንጀል ህጉ ለህጻናት ትኩረት አለመስጠቱ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በፍርድ ቤቶች መልስ ሰጪን ሳያስቀርቡ ይግባኝን መዝጋት...

3135

በመደበኛ ይግባኝ ፍ/ቤቶች እንዲሁም በሰበር ችሎቶች ያለው መልስ ሰጪን ሳያስቀርቡ ይግባኙን መዝጋት ወይም «አያስቀርብም» የሚለው አሠራር በበርካታ የሕግ ባለሙያዎች ቅሬታ የሚቀርብበት አሠራር መሆኑን በመጥቀስ በዘርፉ የተካሔደ አጭር የዳሰሳ ጥናት በፌደራል ጠ/ፍ/ቤት የሕግ ጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ አሮን ደጎል ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

First6162636466686970Last