Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056

ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን  የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ  ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953
Print
1833

Documents to download

  • 252056(.pdf, 838.15 KB) - 259 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

ዜና መግለጫ:- ፌዴራል ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ስለመሆናቸው

2095

ፌዴራል ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ስለመሆናቸው

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 ድረስ ዝግ እንደሚሆኑ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 በአንቀጽ 38 ይደነግጋል፡፡ ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቶች የዜጎች መብቶችን የሚያስከብሩ የፍትህ ተቋማት በመሆናቸው እና የፍርድ ቤት ውሳኔና ትዕዛዝ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ወቅታዊ ምላሽ መስጠት ያስችል ዘንድ ፍርድ ቤቶቹ በከፊል ዝግ ሆነው የሚቆዩ ይሆናል፡፡

የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባላት የትውውቅና የቃለ መሐላ...

2032

የተሻሻለው የፌደራል የዳኝነት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1233/2013 መጽደቁን ተከትሎ አዲስ የተደራጀው የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባላት የትውውቅ እና ቃለ-መሐላ የመፈጸም ሥነሥርዓት ነሐሴ 1 ቀን 2013 ዓ.ም በሒልተን ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ ተካሔደ፡፡

የዳኞች ሥልጠና ፍትሐዊና ተጠያቂነት ያለባቸው ፍርድ...

1836

በፌደራል በጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በዩ.ኤን.ዲፒ (UNDP) መካካል እየተተገበረ ባለው የፍርድ ቤቶች ማሻሻያ ፕሮጀክት አማካኝነት እየተካሄደ በሚገኘው የዳኞች ስልጠና ሥርዓት የዳሰሳ ጥናት ላይ የግብአት ማሰባሰቢያ የውይይት መድረክ ሐምሌ 30 ቀን 2013 ዓ.ም በቤስት ዌስተርን ሆቴል ተካሔደ፡፡

የዳኞችን ዕውቀት እና ክሕሎት በማጎልበት የዳኝነት...

1792

የፌደራል የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓትን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 1183/2012 ላይ ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ከፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለተውጣጡ ዳኞች የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከሐምሌ 24-25 ቀን 2013 ዓ.ም በራዲሰን ብሉ ሆቴል ተሰጠ፡፡

First6263646567697071Last