Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398

የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ ስድስት) ካርቶን የተለያዩ የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ከቻይና ተጓጉዘው ሞጆ ደረቅ ወደብ እስኪደርሱ ድረስ ጉድለትን ጭምሮ ለሚደረስ ማንኛውም ጉዳት በመድን ፖሊስ ቁጥር GU/34/2011/2019/00114 አጠቃላይ የመድህን ሽፋን የሰጣቸው ዕቃዎች ሞጆ ደረቅ ወደብ ደርሰው ከሳሽ ከመረከቡ በፊት ዕቃዎች ገበያ ላይ በመታየታቸው ፍተሻ ተደርጎ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት እንዲፈፀም ህዳር 15 ቀን 2012 ዓ.ም ከሳሽ አቤቱታ አቅርቦ የጉምሩክ ጽ/ቤት ተወካይ፤አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት እና የከሳሽ ማኅበር ተወካዮች በተገኙበት ህዳር 17 ቀን 2012 ዓ.ም ዕቃዎቹ የመጡበት ኮንቴነር ተከፍቶ ሲፈተሸ የዋጋ ግምታቸው ብር 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) የሆነ 171 እሽግ መጉደሉ ተረጋግጦ አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የጎደሉ ዕቃዎችን በዝርዝር በመያዝ ወደ መጋዘኑ ማስገባቱንና ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ አጓዡ ኃላፊነት ወስዶ የጉድለት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ስላልሰጠው የካሳ ክፍያ ጥያቄውን ማስተናገድ አልችልም ማለቱን ጠቅሶ ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ በገባው የማሪን ውል መሰረት የጎደሉ ዕቃዎች ዋጋ 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) ካሳ ማስጠንቀቂያ ከደረሰው ከግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ፤ ከወጪ እና ኪሳራ ጭምር እንዲከፍለው ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942
Next Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Print
1822
«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞችና የአስተዳደር ዘርፍ ክፍል...

2071

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች እና የአስተዳደር ዘርፍ ከፍል ሃላፊዎች በሃገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ባለው “ኢትዮጵያን እናልብስ” ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በመሳተፍ የሃገራችንን የደን ሽፋን የማሳደግና የአየር ንብረትን የመጠበቅ ኃላፊነታችውን ለመወጣት በጉለሌ ዕጽዋት ማዕከል 600 ሃገር በቀል የዛፍ ችግኞችን ተክለዋል፡፡

የፌዴራል ዳኞች የጉባዔ ተወካዮቻቸውን መረጡ

1962

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ የሚወክሏቸውን 3 ዳኞች መረጡ፡፡ የቀድሞውን የዳኞች አስተዳድር ጉባዔ አዋጅ 684/2002ን ለማሻሻል የወጣው የፌዴራል ዳኝነት አስተዳደር አዋጅ 1233/2013 አስራ አምስት ዓባላት ያሉት የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ያቋቋመ ሲሆን በአዋጁ እንቀጽ 6(1/ቀ) መሰረት ከሶስቱም ፌዴራል ፍርድ ቤቶች በዳኞች ጠቅላላ ስብሰባ የተመረጡ አንድ ወንድ እና ሁለት ሴት ዳኞች በድምሩ ሶስት ዳኞች አባል እንዲሆኑ ይደነግጋል፡፡

በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተቋማዊ መዋቅር ላይ ምክክር ተካሄደ

1899

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አመራሮችና የመዋቅር ስራ ክትትልና ቁጥጥር ኮሚቴ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የህገመንግስቱ መጽደቅን ተከትሎ በያዙት አደረጃጀት ተቋማቂ ተልዕኮአቸውን ለመወጣት እንዲያስችላቸው ተግባራዊ በተደረጉ ሶስት ተቋማዊ መዋቅር ላይ ምክክር አካሄዱ፡፡

በቅርቡ የፀደቁ የፍርድ ቤቱን አዋጆች ተግባራዊ ለማድረግ...

1924

ማሻሻያ ተደርጎባቸው በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፀደቁትን የፌደራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/2013 እና የፌደራል ዳኝነት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1233/2013 ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ደንቦችና መመሪያዎች ዝግጅት እየተፋጠነ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡

First6364656668707172Last