Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398

የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ ስድስት) ካርቶን የተለያዩ የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ከቻይና ተጓጉዘው ሞጆ ደረቅ ወደብ እስኪደርሱ ድረስ ጉድለትን ጭምሮ ለሚደረስ ማንኛውም ጉዳት በመድን ፖሊስ ቁጥር GU/34/2011/2019/00114 አጠቃላይ የመድህን ሽፋን የሰጣቸው ዕቃዎች ሞጆ ደረቅ ወደብ ደርሰው ከሳሽ ከመረከቡ በፊት ዕቃዎች ገበያ ላይ በመታየታቸው ፍተሻ ተደርጎ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት እንዲፈፀም ህዳር 15 ቀን 2012 ዓ.ም ከሳሽ አቤቱታ አቅርቦ የጉምሩክ ጽ/ቤት ተወካይ፤አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት እና የከሳሽ ማኅበር ተወካዮች በተገኙበት ህዳር 17 ቀን 2012 ዓ.ም ዕቃዎቹ የመጡበት ኮንቴነር ተከፍቶ ሲፈተሸ የዋጋ ግምታቸው ብር 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) የሆነ 171 እሽግ መጉደሉ ተረጋግጦ አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የጎደሉ ዕቃዎችን በዝርዝር በመያዝ ወደ መጋዘኑ ማስገባቱንና ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ አጓዡ ኃላፊነት ወስዶ የጉድለት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ስላልሰጠው የካሳ ክፍያ ጥያቄውን ማስተናገድ አልችልም ማለቱን ጠቅሶ ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ በገባው የማሪን ውል መሰረት የጎደሉ ዕቃዎች ዋጋ 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) ካሳ ማስጠንቀቂያ ከደረሰው ከግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ፤ ከወጪ እና ኪሳራ ጭምር እንዲከፍለው ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942
Next Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Print
5036
«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

በፌደራል ፍ/ቤቶች የአምስት ዓመት ስትራትጅክ ዕቅድ ላይ...

2705

በፌደራል ፍርድ ቤቶች ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ተግባራዊ እየተደረገ በሚገኘው ስትራቴጅክ ዕቅድ ላይ ከተቀመጡ ስድስት ቁልፍ የውጤት መስኮች አንዱ ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት መሆኑንና በዚህ ውስጥ የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደግብ ተይዞ በዚህ ዙሪያ የተለያዩ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደት ክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ገለጹ፡፡

ፍርድ ቤቱ ከጾታዊ ጥቃት ነጻ የሆነ ማህበረሰብ የመገንባት...

2888

ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከጾታዊ ጥቃት ነጻ የሆነ ማህበረሰብ የመገንባት ዓላማ ያለው መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ገለጹ፡፡

«ጾታን መሰረት አድርገዉ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ከመከላከል አንጻር የአመራሮች ሚና» በሚል ርዕስ ለፌደራል ፍርድ ቤቶች አመራሮችና ሰብሳቢ ዳኞች በቢሾፍቱ ከተማ አዱላላ ሪዞርትና ስፓ ታሕሳስ 25 ቀን 2015 ዓ.ም የተዘጋጀ የስልጠና መርሐ-ግብር ተሒዷል፡፡

ለፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ሠራተኞች በንቃተ-ሕግ እንዲሁም...

2516

ከፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ሬጅስትራሮችና የአስተዳደር ሠራተኞች በንቃተ ሕግና የሴቶች ሰብዓዊ መብቶች በዓለም አቀፍና በኢትየጵያ ሕግ ላይ እንዲሁም ጾታን መሠረት ካደረገ ጉዳት ጋር በተያያዘ በሥነልቦናዊና ማሕበራዊ ድጋፎችና መርሆዎች ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች...

2931

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መቋቋሙን ተከትሎ የሰብዓዊ መብቶችን በሀገራት ለማስረጽና የሕግ ማዕቀፍ ለማበጀት የተለያዩ ሰብዓዊ መብት ስምምነቶችን በማርቀቅ በአባል አገራቱ እንዲጸድቅ ማድረጉንና ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች በአገራችን ላይ ስምምነቶቹን የማክበር፣ የማስከበር እና ሰብአዊ መብቶችን የማሟላት ግዴታ እንደሚጥሉባት ተጠቆመ፡፡

First6364656668707172Last