የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ የሚወክሏቸውን 3 ዳኞች መረጡ፡፡ የቀድሞውን የዳኞች አስተዳድር ጉባዔ አዋጅ 684/2002ን ለማሻሻል የወጣው የፌዴራል ዳኝነት አስተዳደር አዋጅ 1233/2013 አስራ አምስት ዓባላት ያሉት የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ያቋቋመ ሲሆን በአዋጁ እንቀጽ 6(1/ቀ) መሰረት ከሶስቱም ፌዴራል ፍርድ ቤቶች በዳኞች ጠቅላላ ስብሰባ የተመረጡ አንድ ወንድ እና ሁለት ሴት ዳኞች በድምሩ ሶስት ዳኞች አባል እንዲሆኑ ይደነግጋል፡፡