Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
6109

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 857 download(s)

«May 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
27282930123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031
1234567

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ እና...

2449

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅዳቸውን እና የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ሶስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የተመለከተ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና ዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም ማብራሪያ አቀረቡ፡፡

ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ግዥን በዕውቀት ሊመሩት...

2482

የግዥን ጉዳይ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በዕውቀት ሊመሩት ይገባል ሲሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ገለፁ፡፡

በመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አዘጋጅነት ለዳኝነት አካላት በአርባ ምንጭ ከተማ ሲሰጥ በነበረው ስልጠና ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ምክትል ፕሬዝዳንቱ በአብዛኛው በከፍተኛ አመራሮች ላይ የሚቀርቡ የሙስና ወንጀል ክሶች ከግዥ ጋር የተያያዙ በመሆናቸው ከፍተኛ አመራሮች ግዥን በዕውቀት ሊመሩት ይገባል ብለዋል፡፡

 

የሌሎችን  የሥነምግባር ችግር ከሚዳኘው የዳኝነት ተቋም...

2405

ሕብረተሰቡ ከዳኞች የሚጠብቀውን የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት መጀመሪያ ዳኞች በላቀ የሥነምግባር ደረጃ ላይ ሊገኙ እንደሚገባ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ብርሐነመስቀል ዋጋሪ ገለጹ፡፡

ከፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች በፌዴራል ዳኞች ሥነምግባርና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ላይ ለሁለተኛ ዙር በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከመስከረም 14-15 ቀን 2014 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው ቲኬ ኢንተርናሽናል ሆቴል ተሰጥቷል፡፡

ክቡር ፕሬዚደንቱ በግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በፍርድ ቤቶች ከትናንት ይልቅ ዛሬ የዳኝነት ነጻነትና ተጠያቂነት አተገባበር እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቁመው ይህንም በፍ/ቤቶች ረዘም ያለ ቆይታ ያላቸው ዳኞች የሚገነዘቡት ነው ብለዋል፡፡

የፍርድ ቤቱ ሠራተኞች ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀንን አከበሩ

2442

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ23ኛ ጊዜ በመከበር ላይ የሚገኘው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ “በትዉልድ ቅብብሎሽ ኢትዮጵያ ትፀናለች” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኝ ሲሆን ቀኑ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሠራተኞች ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ/ም በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ፡፡

በዓሉ በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ሲከበር የፍርድ ቤቱ ሴቶችና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ወርቅነሽ በቀለ ባደረጉት የመክፈቻ ላይ ንግግር እንደገለጹት ከሰባት ቢሊዮን በላይ ከሚገመተዉ የዓለም ህዝብ መካከል የወጣቱ ቁጥር 1.8 ቢሊዮን እንደሚደርስና ከዚህ ውስጥ 90 ከመቶ የሚሆነዉ ወጣት በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት እንደሚገኝ ጠቅሰው ከሀገራችን የህዝብ ብዛትም 31.8 በመቶ ያህሉ ከፍተኛ አቅም ያለዉ አምራች ኃይል የሆነዉ የወጣቱ ክፍል መሆኑን አስረድተዋል፡፡

First6364656668707172Last