Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230

የአሁን አመልካች በምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ/መ/ቁ 47863 እና በመ/ቁ በመ/ቁ 47862 በሁለቱም መዝገቦች ላይ 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው የክስ ይዘትም አመልካች የኢትዮጵያ የፌዴራል ቡና እና ሻይ ባለስልጣን ግምቢ ቅርንጫፍ የቡና ላኪ ሸኚ ስምሪት ጣቢያ ላይ ቋሚ ሰራተኛ ሆኖ በባለሙያነት ተቀጥሮ እየሰራ እያለ በቡና ንግድ ውስጥ የማጭበርበር ድርጊት በመፈጸም ለራሱ የማይገባውን ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ በምዕራብ ወለጋ ዞን ግምቢ ከተማ ቀበሌ 05 በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ግምቢ ቅርንጫፍ ግቢ ውስጥ ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም  ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርብ የተቀሸረ ቡና ዓይነቱ እና የሰሌዳ ቁጥሩ 3-A02958 A.A በሆነ ኤፍ.ኤስ፣አር መኪና ከነጆ ከተማ ተጭኖ በፕሎምፕ ታሽጎ የቡናው ፕሎምፕ ቁጥር GM-7 በሚባል የታሸገውን በሚልክበት ጊዜ የቡናውን መጠን አጣርቶ መላክ እያለበት የተቀሸረ 129 ኩንታል ተጭኖ እያለ 100 ኩንታል በሚል እንዲሁም ከአይራ ወረዳ  በሲኖ ትራክ 210 ኩንታል ቡና የተጫነ ነዉ ተብሎ የተላከዉን ተቀብሎ በቡናው የይለፍ ወረቀት ላይ ይህንኑ መጠን በማረጋገጥ የይለፍ ወረቀት ከሰጠ በኋላ በዚሁ ቀን የተጠቀሱት መኪናዎች  በጊምቢ ከተማ ልዩ ስሙ ሰርጤ ኬላ ቦታ ላይ በቁጥጥር ስር ውለዉ ሲፈተሹ 29 እና 70 ኩንታል ቡና እንደቅደም ተከተላቸዉ  ከህግ ውጭ ጥራት በሌለው የማዳበሪያ ከረጢት ተጨምሮ እሱ በይለፍ ወረቀት ላይ ጽፎ ከሰጠው በላይ በተጨማሪ ተጭኖ ስለተገኘ የአዋጅ 1051/2009 አንቀጽ 19/5/ የሚኒስትሮች ም/ቤት ደንብ ቁጥር 433/2007 አንቀጽ 41(1)(ቀ) በመተላለፍ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት አስቦ በቡና ንግድ ውስጥ የማጭበርበር ወንጀል ድርጊት ፈጽሟል የሚል ነው፡፡ መልካም ምንባብ…

Previous Article አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395
Next Article ወ/ሮ የማርውሃ ወርቅነህ እና እነ ወ/ሮ ዓለም ወርቅነህ የሰ.መ.ቁ 242314
Print
7251

Documents to download

  • 267231(.pdf, 1.08 MB) - 1472 download(s)

«August 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
31123456

የወንጀል ህጉ ለህጻናት ትኩረት አለመስጠቱ ከህጻናት ጋር...

3061

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የተቋቋመዉ የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የካቲት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በሕጻናት ጉዳይ ላይ ለሚሰሩ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት፣ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዳኞችና ለሶሻል ወርክ ባለሙያዎች ባዘጋጀዉ የሥልጠና መድረክ ላይ ከህጻናት ጋር ተያያዥነት ላላቸዉ ወንጀሎች መበራከት ዋነኛ መንስኤዉ የወንጀል ህጉ ለህጻናት ትኩረት አለመስጠቱ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በፍርድ ቤቶች መልስ ሰጪን ሳያስቀርቡ ይግባኝን መዝጋት...

3383

በመደበኛ ይግባኝ ፍ/ቤቶች እንዲሁም በሰበር ችሎቶች ያለው መልስ ሰጪን ሳያስቀርቡ ይግባኙን መዝጋት ወይም «አያስቀርብም» የሚለው አሠራር በበርካታ የሕግ ባለሙያዎች ቅሬታ የሚቀርብበት አሠራር መሆኑን በመጥቀስ በዘርፉ የተካሔደ አጭር የዳሰሳ ጥናት በፌደራል ጠ/ፍ/ቤት የሕግ ጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ አሮን ደጎል ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ለቀድሞዎቹ የፍ/ቤቱ ፕሬዚደንት እና ም/ፕሬዚደንት...

3852

ለቀድሞዎቹ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት እና ም/ፕሬዚደንት ለክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊና ለክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ የካቲት 11 ቀን 2015 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል አሸኛኘት ተደረገላቸው፡፡

አሸኛኘቱን ያደረጉት አዲስ የተሾሙት የፍ/ቤቱ ፕሬዚደንት እና ም/ፕሬዚደንትነት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምሕረት እና ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለን ጨምሮ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና የሶስቱም የፌደራል ፍ/ቤቶች አመራሮች ናቸው፡፡

First6364656668707172Last