Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056

ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን  የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ  ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….

Previous Article የፌደራል ዐቃቤ ህግ እና አቶ አበበ ወንድሙ ኤጋ የሰ/መ/ቁጥር 251759
Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953
Print
4989

Documents to download

  • 252056(.pdf, 838.15 KB) - 567 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

ጾታን መሠረት ባደረጉ የኃይል ጥቃቶች 90 በመቶ ያህል...

2911

በአገራችን ጾታን መሠረት አድርገው ከሚፈጸሙ የኃይል ጥቃቶች መካከል 90 በመቶ ያህል ጥቃት ፈጻሚዎች ለፍትሕ ተቋማት ቀርበው ሕጋዊ ቅጣት እንደማያገኙ ተመለከተ፡፡

ጾታን መሰረት ያደረጉ የኃይል ጥቃቶች የወንጀል ምርመራ ቴክኒኮች፣ ፕሮቶኮል እንዲሁም አሠራሮችን በሚመለከት ለፌደራል ዳኞች እና ሌሎች የዳኝነት አካላት ሕዳር 17 እና 18 ቀን በአዳማ ከረዩ ሪዞርት ሆቴል ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት...

3053

Meaza Ashenafi, who is best recognized for her work to empower women, was elected as the Federal Supreme Court’s first female president. She has held this role ever since, leading numerous initiatives to modernize the justice system. It wasn’t an easy task, especially in a nation where the separation between the three branches of government—the Executive, the Legislature, and the Judiciary—is blurred.

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዚደንቶች፣ አመራሮችና ዳኞች...

2382

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የክርክር ፍርድ ቤት የግማሽ ጊዜ ዳኛ ሆነው መሾማቸውን ምክንያት በማድረግ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዚደንቶች፣ ዳኞችና የሥራ ኃላፊዎች ሕዳር 13 ቀን 2015 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ የእንኳን ደስ አለዎት መርሐ-ግብር አካሔዱ፡፡

በፌደራል ፍርድ ቤቶች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ እና...

2587

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የ2015 በጀት ዓመት ዕቅዳቸውን እና የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ሶስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የተመለከተ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና ዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም ማብራሪያ አቀረቡ፡፡

First6465666769717273Last