Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947

ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ በማህበር በመደራጀት ከተገኘዉ ይዞታ ጋር የተያያዘ ሲሆን አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት  ክስ በ03/08/1990 ዓ/ም ተመዝግቦ በፀደቀዉ የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የተደራጀ ታቦር የመኖሪያ ቤቶች ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል በመሆን ተደራጅተዉ ማኅበሩ በሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ካገኘዉ ጠቅላላ ይዞታ ላይ መጠኑ 203.67 ካሬ ሜትር የሆነዉን የክርክሩን ይዞታ   በድርሻ እንደሰጣቸዉና የዚሁ ይዞታ ሕጋዊ ባለመብት ስለመሆናቸዉም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 281839 በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤትና በኮልፌ  ቀራኒዮ ክለ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት ላይ ክስ አቅርበዉ መብታቸዉ ተረጋግጦ ዉሳኔ እንዲያገኝ የሚል ነው፡መልካም ንባብ…

Previous Article ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243
Next Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Print
2090

Documents to download

  • 259947(.pdf, 828.26 KB) - 364 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች...

2430

በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ ትግበራ ማስጀመሪያ ውይይት ተካሄደ

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቶችን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሚረዳ የፍትሃ ብሔር ጉዳዩች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ በሚያዚያ ወር 2013 ዓ.ም ማውጣቱን ተከትሎ የመመሪያውን ትግበራ በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለማስጀመር የሚያስችል ውይይት ሰኔ 19 ቀን 2013 ተካሄደ፡፡

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ...

2169

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሚካሄድበት ዕለት በከፊል ክፍት ሆነው ይውላሉ፣

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሚካሄድበት ዕለት ሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከምርጫ ጋር የተያያዙ እና አጣዳፊ የፍርድ ቤት ውሳኔ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ለማስተናገድ በከፊል ክፍት  እንደሚሆኑ ተገለጸ።

በፍትሃ ብሔር ፍርደ አፋጻጸም በሚታዩ ተግዳሮቶች እና...

1974

ሰኔ 6 ቀን 2013 ዓ.ም/ ቢሸፍቱ/ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በፍትሃ ብሔር ጉዳዮች ላይ የሚሰጧቸውን ውሳኔዎችና ትእዛዞችን በማስፈጸም ሂደት በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችና ሊወሰዱ በሚገቡ የማስትካከያ እርምጃዎች ላይ ከባልድርሻ እካላት ጋር ምክክር አደረገ።

በረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የአስተዳደር ሰራተኞች...

2228

በረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የአስተዳደር ሰራተኞች ግብአት የሚሰጡበት ሁኔታ መመቻቸቱ  ሰራተኞች በፍርድ ቤቶች የማሻሻያ ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ እንዲሚያሰፋው ተገለጸ፡፡

 

ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች የተውጣጡ የአስተዳደር ሰራተኞች በአማካሪ ድርጅቱ በመዘጋጀት ላይ ባለው ረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ተጨማሪ ግብአት እንዲሰጡ ሁኔታዎች መመቻቸታቸው የአስተደደር ሰራተኞች በፍርድ ቤቶች በመተግበር ላይ ባለው የማሻሻያ ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ እንደሚያሰፋ ገለጹ፡፡

First6465666769717273Last