Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
2655

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 485 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች...

2430

በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ ትግበራ ማስጀመሪያ ውይይት ተካሄደ

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቶችን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሚረዳ የፍትሃ ብሔር ጉዳዩች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ በሚያዚያ ወር 2013 ዓ.ም ማውጣቱን ተከትሎ የመመሪያውን ትግበራ በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለማስጀመር የሚያስችል ውይይት ሰኔ 19 ቀን 2013 ተካሄደ፡፡

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ...

2169

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሚካሄድበት ዕለት በከፊል ክፍት ሆነው ይውላሉ፣

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሚካሄድበት ዕለት ሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከምርጫ ጋር የተያያዙ እና አጣዳፊ የፍርድ ቤት ውሳኔ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ለማስተናገድ በከፊል ክፍት  እንደሚሆኑ ተገለጸ።

በፍትሃ ብሔር ፍርደ አፋጻጸም በሚታዩ ተግዳሮቶች እና...

1974

ሰኔ 6 ቀን 2013 ዓ.ም/ ቢሸፍቱ/ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በፍትሃ ብሔር ጉዳዮች ላይ የሚሰጧቸውን ውሳኔዎችና ትእዛዞችን በማስፈጸም ሂደት በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችና ሊወሰዱ በሚገቡ የማስትካከያ እርምጃዎች ላይ ከባልድርሻ እካላት ጋር ምክክር አደረገ።

በረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የአስተዳደር ሰራተኞች...

2228

በረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የአስተዳደር ሰራተኞች ግብአት የሚሰጡበት ሁኔታ መመቻቸቱ  ሰራተኞች በፍርድ ቤቶች የማሻሻያ ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ እንዲሚያሰፋው ተገለጸ፡፡

 

ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች የተውጣጡ የአስተዳደር ሰራተኞች በአማካሪ ድርጅቱ በመዘጋጀት ላይ ባለው ረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ተጨማሪ ግብአት እንዲሰጡ ሁኔታዎች መመቻቸታቸው የአስተደደር ሰራተኞች በፍርድ ቤቶች በመተግበር ላይ ባለው የማሻሻያ ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ እንደሚያሰፋ ገለጹ፡፡

First6465666769717273Last