Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947

ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ በማህበር በመደራጀት ከተገኘዉ ይዞታ ጋር የተያያዘ ሲሆን አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት  ክስ በ03/08/1990 ዓ/ም ተመዝግቦ በፀደቀዉ የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የተደራጀ ታቦር የመኖሪያ ቤቶች ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል በመሆን ተደራጅተዉ ማኅበሩ በሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ካገኘዉ ጠቅላላ ይዞታ ላይ መጠኑ 203.67 ካሬ ሜትር የሆነዉን የክርክሩን ይዞታ   በድርሻ እንደሰጣቸዉና የዚሁ ይዞታ ሕጋዊ ባለመብት ስለመሆናቸዉም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 281839 በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤትና በኮልፌ  ቀራኒዮ ክለ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት ላይ ክስ አቅርበዉ መብታቸዉ ተረጋግጦ ዉሳኔ እንዲያገኝ የሚል ነው፡መልካም ንባብ…

Previous Article ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243
Next Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Print
2995

Documents to download

  • 259947(.pdf, 828.26 KB) - 455 download(s)

«January 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2930311234
567891011
12131415161718
19202122232425
2627282930311
2345678

በአገልግሎት አሰጣጥና የደንበኞች አያያዝ ላይ ሲሰጥ...

519

የፌደራል የህግና የፍትሕ ኢንስቲትዩት ለተከታታይ ሦስት ሳምንታት በሶስት ዙር ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች፣ከፍትሕ ሚኒስቴር እንዲሁም ከፌዴራል የሕግና የፍትሕ ኢንስቲትዩት ለተውጣጡ 170 የአስተዳደር ሰራተኞች ከጥቅምት 21 ቀን እስከ ህዳር 6ቀን 2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል፡፡

የተግባር ልምምድ (ስልጠና) በዲጂታል የዳኝነት አገልግሎት...

467

በዲጂታል የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከቀን 06-07/03/2018 ዓ.ም ለሁለት ቀናት የሚቆይ የተግባር ልምምድ (ስልጠና) ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች እየተሰጠ ይገኛል።

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሪሶርስ ኢንሪቺንግ አፍሪካን...

370

ሪሶርስ ኢንሪቺንግ አፍሪካን ላይቭስ በመባል የሚጠራ ግብረ ሰናይ ድርጅት ቡክስ ፎር አፍሪካና ቶምሰን ሪዉተርስ ከሚባሉ ለጋሽ ድርጅቶች ለትምህርት ቤቶች እና ለፍትህ ተቋማት የሚያገለግሉ መጻሃፍቶችን በማሰባሰብ ወደ አገር ውስጥ እንዲገባ አድርጓል፡፡

በአስማሚነት ክህሎት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረዉ የተግባር...

552

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት ከጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ 4 ቀናት በተግባር ሲሰጥ የነበረዉ የአስማሚነት ክህሎት ስልጠና ተጠናቋል፡፡

First2345791011Last