Selam Warga / Tuesday, June 17, 2025 / Categories: CASSATION, Cassation ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594 የጉዳዩ አመጣጥ ተጠሪ ለአመልካች በቁጥር ማዕ/ሠ831በ/1/2 በ4/11/2015ዓ.ም በተጻፈ በቁጥር ማዕ/ሠ831በ/1/1 በ9/10/2015 በተጻፈ የምደባ ደብዳቤ ላይ የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ውስጥ በደረጃ XVIII በመደብ ማስታወቂያ ቁጥር 13/ግብ-1094 የስራ መደብ መጠሪያ የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሆነው መመደባቸውን በመግለጽ ሆኖም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሰራተኞች ምደባ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ከአመልካች ጋር የተወዳደሩት ተወዳዳሪው የትምህርት ደረጃ በዲፕሎማ የእንስሳት እርባታ (Animal Production and Rangeland management) ይዘው የልማት ጣቢያ ሰራተኛ ሆነው የሰሩት የስራ ልምድ አያያዝ ትክክል አይደለም በማለት ባቀረቡት ቅሬታ ላይ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴው ቅሬታው ተገቢ መሆኑን ተገንዝቦ ምደባው እንዲስተካከል በወሰኑት ውሳኔ መሰረት አመልካች የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሆነው የተመደቡበት የስራ ምደባ ከሀምሌ 1 ቀን 2015ዓ.ም ጀምሮ ተነስቷል በማለት በጻፈው ደብዳቤ ያሳለፈውን ውሳኔ አመልካች በመቃወም ለየኢፌዲሪ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አስተዳደር ፍርድቤት ባቀረቡት ይግባኝ ያለኝ ዲፕሎማ እንስሳት እርባታ (Animal Production and RangeLand Management) ቢሆንም የተቀጠርኩት እና ለ6 አመት ያገለገልኩት ግን ሁሉንም የግብርና ሙያ ድጋፍ ማድረግ የሚችል አጠቃላይ እርሻ ዲፕሎማ ሙያ በሚጠይቀው ማለትም 2ኛ እና 1ኛ ደረጃ ሁለገብ ልማት ጣቢያ ሰራተኛ እንደቅደም ተከተሉ ነው፡፡መልካም ንባብ…. Previous Article አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947 Next Article አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395 Print 2606 Documents to download 260594(.pdf, 874.35 KB) - 407 download(s)
የቪድዮ ኮንፍረንስ፣ ኢ- ፋይሊንግ እና ዳታቤዝ አገልግሎት... የቪድዮ ኮንፍረንስ፣ ኢ- ፋይሊንግ እና ዳታቤዝ አገልግሎት... Friday, September 5, 2025 718 የቪድዮ ኮንፍረንስ፣ ኢ- ፋይሊንግ እና ዳታቤዝ አገልግሎት በደቡብ ምዕራብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤ፣ ቦንጋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንዲሁም በዞን ፍርድ ቤቶች በአጠቃላይ በ35 ፍርድ ቤቶች በቀን 30/12/2017 ዓ.ም በይፋ ተጀምሯል፡፡ Read more
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኘሬዝዳንት ክቡር አቶ... በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኘሬዝዳንት ክቡር አቶ... Friday, September 5, 2025 519 ልዑክ ቡድኑ ሆሳዕና ከተማ ሲገቡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በጽ/ቤታቸው የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ Read more
የፍርድ ቤቶች ዲጅታላይዜሽን እና አዲሱን መመሪያ... የፍርድ ቤቶች ዲጅታላይዜሽን እና አዲሱን መመሪያ... Friday, September 5, 2025 565 ፌዴራል ፍ/ቤቶችን በራሳቸዉ ኔትወርክ የማስተሳሰር እና አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ መሰረት ይሆን ዘንድ ላለፉት ዓመታት ፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት እያስገነባ የነበረዉ ክላዉድ የመረጃ ቋት ያለዉ እና ደህንነቱ የተረጋገጠ የዋይድ ኤሪያ ኔትወርክ መሰረተ ልማት ዝርጋታ እየተጠናቀቀ ይገኛል። Read more
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኘሬዝዳንት ክቡር አቶ... በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኘሬዝዳንት ክቡር አቶ... Tuesday, September 2, 2025 662 በጉብኝታቸውም የ2017 ዓ.ም በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በክልሉ ፍርድ ቤቶች የተጀመሩ የለውጥ ስራዎችን በተመለከተ በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ደምሴ ዱላቻ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡ Read more
12Dec2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ የሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Friday, December 12, 2025 Read more
6Nov2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Thursday, November 6, 2025 Read more
8Oct2025 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት ውስጥ ሚገኝ የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ Wednesday, October 8, 2025 Read more