Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰበር መዝገብ ቁጥር 266395

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው 1ኛ ክስ የወ/ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 34(1) እና 693(1) በመተላለፍ በትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ውስጥ የፋብሪካው ኃላፊ እና ባለንብረት ሆኖ በሚሰሩበት ጊዜ ለግል ተበዳይ አቶ ሸምሱ አወል የብር አምስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺህ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የሚመነዘር ቼክ ሰጥቶ የግል ተበዳይ ገንዘቡን ለማውጣት ወደ ባንክ ሲሄድ በቂ ገንዘብ የለውም በመባሉ ገንዘቡን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ስለዚህ በቂ ስንቅ ሳይኖር ቼክ በመስጠት ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡ አመልካች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ በመከራከሩ ተጠሪ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቦ እንደ ክስ አቀራረቡ አስረድቷል፡፡ አመልካች እንዲከላከል ታዞ መከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ሲሆን የአመልካች መከላከያ ምስክሮች ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቼክ መጥፋቱን አስረድተዋል፡፡መልካም ንባብ…. 

Previous Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Next Article ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 267231፣267230
Print
2650

Documents to download

  • 266395(.pdf, 849.74 KB) - 485 download(s)

«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

ፍርድ ቤቱ ባቀረበው የበጀት ጥያቄ ላይ በምክር ቤቱ...

2211

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን የ2014 በጀት ዓመት የበጀት ፍላጎት ለኢፌዲሪ ሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ማቅረቡን ተከትሎ በበጀት ፍላጎት ላይ ለተነሱ ማብራሪያ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች መግለጫ ሰጠ፡፡

የተማሪዎችን የሕግ ግንዛቤ ለማሳደግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ

2678

በትምህርት ቤቶችና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች ያላቸውን የሕግ ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ በትምሕርት ሚኒስቴር፣ በሳይንስና ከፍተኛ ትምሕርት ሚኒስቴር እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መካከል ተፈረመ፡፡

ለስትራቴጂካዊ ዕቅድ ዝግጅት የተካሄዱ የትንተና ጥናቶች...

2350

በአማካሪ ድርጅት የሚሰራውን ሶስተኛው የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ዝግጅት ሂደትን እንዲከታተል በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተቋቋመው ዓብይና የቴክኒክ ኮሚቴ አማካሪ ድርጅቱ ለስትራቴጂካዊ ዕቅድ ዝግጅት ባካሄዳቸው የትንተና ጥናቶች ላይ ተጨማሪ ግብዓት ሰጠ፡፡

ፍርድ ቤቶች በዘጠኝ ወሩ ከአንድ መቶ 19 ሺህ በላይ...

2376

የፌደራል ፍርድ ቤቶች በ2013 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ለ119, 413 መዛግብት እልባት መስጠታቸውን የሶስቱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የተጠቃለለ የዘጠኝ ወር የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አመለከተ፡፡

First6667686971737475