Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

እነ ወ/ሮ ዘውዲቱ ድንቁ(2ሰዎች)የቀድሞ አርጋፋ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት (በአሁን አርጋፋ ማዘጋጃ ቤት)የሰ/መ/ቁ፡- 250597

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች ሐምሌ 03 ቀን 2015ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ.ቁ 26960፤ ጥቅምት 28 ቀን 2015 የሰጠው ውሳኔ እና ይህንኑ ውሳኔ በማጽናት የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 42102፤ ሚያዝያ 03 ቀን 2015ዓ.ም መወሰኑ የመሠረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረባቸው ነው፡፡

ጉዳዩ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 6 መሠረት የቀረበን የዳግም ዳኝነት ጥያቄን የሚመለከት ሲሆን ከመነሻው በዋናው ጉዳይ ክርክር የተጀመረው በኦሮሚያ ክልል አጋርፋ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን አመልካች ከሳሽ፤ የአሁን ተጠሪ ተከሳሽ ነበሩ፡፡መልካም ንባብ…..

Previous Article አቶ ኩማ መልኩ እና አቶ ሰለሞን ዘለቀ የሰበር መ/ቁ/250546
Next Article ደጀኔ ደበላ አልቀረበም እና ኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 251700
Print
4867

Documents to download

  • 250597(.pdf, 850.17 KB) - 608 download(s)

«May 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
27282930123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031
1234567

«የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ እና የወደፊት...

3056

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ «የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ እና የወደፊት ዕይታ /State of the Judiciary/» በሚል ርዕስ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀ ጉባዔ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ የካቲት 6 ቀን 2014 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

የመጀመሪያው ጉባዔ በ2012 የተካሔደ ሲሆን መድረኩ በኮቪድ 19 ምክንያት ተቋርጦ ከቆየ በኋላ ሁለተኛው ጉባዔ በፌደራል ፍርድ ቤቶች በ2013 በጀት ዓመት እና በ2014 ግማሽ በጀት ዓመት በተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ተከናውኗል፡፡

የቅድመ መዋቅር ነባራዊ ሁኔታ ትንተና  እና ረቂቅ ተቋማዊ...

2987

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተቋማዊ መዋቅርን እንዲሰራ በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት - በፍትህ ፕሮጀክት የተቀጠረ እማካሪ ድርጅት ያካሄደውን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ነባራዊ ሁኔት ትንተና ውጤት በፍርድ ቤቱ በኩል ስራውን እንዲከታተል ለተቋቋመ አብይ ኮሚቴ አቀረበ።

አማካሪ ድርጅቱ ( HST) ቀደም ሲል እያካሄደ ያለውን ጥናት በተደጋጋሚ ለዐብይ ኮሚቴው በማቅረብና የጥናት ስልት፣ ሂደት፣ ይዘት እና ወስን ላይ የማዳበሪያ እና አቅጣጫ ጠቋሚ ሃሳቦችን ሰብስቧል።

የዳኝነት ስርዓቱን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ፍርድ ቤቱ...

2667

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት ስርዓቱን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት በቅርቡ ከተቋቋመው የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ገለጹ፡፡

ክቡር አቶ ሰለሞን ይህን የገለጹት በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው በአዲሱ የፌደራል የጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ መሰረት ለተቋቋመው የጠበቆች ማህበር ስራ ማስጀመሪያ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በእንግድነት ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው፡፡

ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ በሰጡት የማጠቃለያ አስተያየት...

2258

ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ (የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንት) ጥር 9 ቀን 2014 ዓ.ም «ፍርድ ቤቶች እና የሽግግር ፍትሕ፤ ግጭቶች ሲከሰቱ ወይም ከግት በኋላ» በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ሲምፖዚየም ላይ ከተሳታፊዎች የቀረቡ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ በሰጡት የማጠቃለያ አስተያየት ካነሷቸው ነጥቦች መካከል ዋና ዋናዎቹ፡-

• ሲምፖዚየሙን ማዘጋጀት ያስፈለገው አሁን አገራችን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ የዳኝነት ተቋሙ ሊኖረው ከሚችለው የዳኝነት ሚና ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡

First7071727375777879Last