Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947

ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ በማህበር በመደራጀት ከተገኘዉ ይዞታ ጋር የተያያዘ ሲሆን አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት  ክስ በ03/08/1990 ዓ/ም ተመዝግቦ በፀደቀዉ የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የተደራጀ ታቦር የመኖሪያ ቤቶች ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል በመሆን ተደራጅተዉ ማኅበሩ በሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ካገኘዉ ጠቅላላ ይዞታ ላይ መጠኑ 203.67 ካሬ ሜትር የሆነዉን የክርክሩን ይዞታ   በድርሻ እንደሰጣቸዉና የዚሁ ይዞታ ሕጋዊ ባለመብት ስለመሆናቸዉም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 281839 በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤትና በኮልፌ  ቀራኒዮ ክለ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት ላይ ክስ አቅርበዉ መብታቸዉ ተረጋግጦ ዉሳኔ እንዲያገኝ የሚል ነው፡መልካም ንባብ…

Previous Article ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243
Next Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Print
2512

Documents to download

  • 259947(.pdf, 828.26 KB) - 417 download(s)

«December 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
24252627282930
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
2930311234

የአዋጅ መሻሻልን ተከትሎ በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት...

2762

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 25/88 እና ሌሎች ተከታታይ የአዋጁ ማሻሻያዎችን በመሻር በጥር ወር 2013 ዓ.ም  በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የጸደቀው አዲስ አዋጅ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍትሐ ብሔር ስረ-ነገር ሥልጣን ላይ ለውጥ ማድረጉን ተከትሎ በፌዴራል መጀመሪያ ድረጃ ፍርድ ቤት ሊኖር ስለሚችል የችሎት አደረጃጀት እና የዳኞች አሰያየምን ለማመላከት የተካሄደ የዳሰሳ ጥናት ውጤት ሚያዚያ 15 ቀን 2013 ዓ.ም ለፍ/ቤቱ አስተባባሪ ዳኞች፤ ዳኞች፣ ለሬጂስትራሮችና ለልዩ ልዩ የስራ ክፍል ኃላፊዎች ለአስተያየት ቀረበ፡፡

የፌዴራል ፍ/ቤቶች ከፍተኛ አመራር እንዲያጸድቅ በቀረቡለት...

2705

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶችና ም/ፕዝደንቶች ሚያዚያ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ እንዲያጸድቃቸው በቀረቡለት የፍትሃብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር ረቂቅ መመሪያ እና የተሸሻለውን የCCMS (Court Case Management System) ለመተግበር የሚያስችል የስራ መዘርዝር እና ፍሰት የሚገልጽ ሰነድ ላይ ተወያየ፡፡

የስትራቴጂካዊ ዕቅድ ዝግጅት አማካሪ ድርጅት ዕቅድ ዝግጅቱ...

2570

የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን 3ኛ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ለማዘጋጀት በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተቀጠረው ጥምር አማካሪ ድርጅት በጽንሰ ጥናት ሪፖርቱ ባስቀመጠው የድርጊት መርሃ ግብር መሰረት የዕቅድ ዝግጅት ስራው ያለበትን ደረጃ በፍርድ ቤቱ በኩል ስራውን እንዲከታተልና አስፈላጊ ግብአቶችን እንዲያቀርብ ሃላፊነት ለተሰጣቸው ዐብይ እና ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት ዛሬ ሚያዚያ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ገለጸ፡፡

በጠቅላይ ፍርድ ቤት የምርጫ ጉዳዮችን እንዲመለከቱ...

2390

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ከምርጫ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች የሚታዩባቸው ችሎቶች በጠቅላይ ፍ/ቤት መደራጀታቸውን አፈጻጸማቸውን በተመለከተ ለፕሬዝደንት ጽ/ቤትና ለሬዲስትራሮች የስራ አቅጣጫ ሰጡ፡፡ 

First6869707172737577