Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

እነ ወ/ሮ ዘውዲቱ ድንቁ(2ሰዎች)የቀድሞ አርጋፋ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት (በአሁን አርጋፋ ማዘጋጃ ቤት)የሰ/መ/ቁ፡- 250597

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች ሐምሌ 03 ቀን 2015ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ.ቁ 26960፤ ጥቅምት 28 ቀን 2015 የሰጠው ውሳኔ እና ይህንኑ ውሳኔ በማጽናት የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 42102፤ ሚያዝያ 03 ቀን 2015ዓ.ም መወሰኑ የመሠረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረባቸው ነው፡፡

ጉዳዩ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 6 መሠረት የቀረበን የዳግም ዳኝነት ጥያቄን የሚመለከት ሲሆን ከመነሻው በዋናው ጉዳይ ክርክር የተጀመረው በኦሮሚያ ክልል አጋርፋ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን አመልካች ከሳሽ፤ የአሁን ተጠሪ ተከሳሽ ነበሩ፡፡መልካም ንባብ…..

Previous Article አቶ ኩማ መልኩ እና አቶ ሰለሞን ዘለቀ የሰበር መ/ቁ/250546
Next Article ደጀኔ ደበላ አልቀረበም እና ኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 251700
Print
4867

Documents to download

  • 250597(.pdf, 850.17 KB) - 608 download(s)

«May 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
27282930123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031
1234567

ባለፉት ሶስት ዓመታት በተከናወኑ የማሻሻያ ስራዎች ተስፋ...

2994

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች እየተከናወኑ ባሉ የማሻሻያ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መገኘታቸውን የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዳኞችና የአስተዳደር ዘርፍ ሃላፊዎች እንዲሁም የስር ፍርድ ቤቶች ፕዝደንቶችና ም/ፕሬዝደንቶች በተገኙበት በተካሄደ የውይይት መድረክ ላይ ገለጹ፡፡

የውይይት መድረኩ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ከጀስቲስ ፎር ኦል- ፐሪዝን ፌሎው ሺፕ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ ሂደት የፍርድ ቤቶች ሚናን አስመልክቶ ዳኞች በሙያቸው ያገኙትን ዕውቀትና እና አመለካከት እርስ በእርስ እንዲለዋወጡ ማስቻል እና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማሻሻያ ስራዎች ያስገኙትን ውጤት መገምገም ዓላማ ያደረገ ነው፡፡

ፍርድ ቤቱ በስትራቴጂያዊ እና ዓመታዊ ዕቅዱ ላይ ለምክር...

3141

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ ፍትህና የዲሞክራሲ ጉዳዩች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ፍርድ ቤቱ ባዘጋጀው ሶስተኛው ስትራቴጂያዊ ዕቅድ እና ዓመታዊ ዕቅድ ላይ ማብራሪያ ሰጠ፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ በፍርድ ቤቱ በኩል ዕቅዶቹን አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያ ከመቅረቡ በፊት በሰጡት አጭር ገለጻ የዳኝነት ዘርፉ በአማካሪ ድርጅት በመታገዝ ስትራቴጂያዊ ዕቅዱን ማዘጋጀቱን፤ የዕቅዱን ይዘትና አዘገጃጀት ሂደት የሚከታተል በየደረጃ ያሉ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ የስራ ክፍል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች አባል የሆኑባቸው ዓቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ መቋቋማቸውን፤ በረቂቅ ዕቅዱ ላይ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማህበረሰብ እና ባለድርሻ አካላት መወያየታቸውን እና የተገኙ ተጨማሪ ግብዓቶችን በማካተት ተዘጋጅቶ የጸደቀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሙስና ወንጀልን በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል...

2895

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጃ ታደሰ የሙስና ወንጀልን በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል እንደሚገባ ገለጹ፡፡

አቶ ቦጃ ታደሰ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዓል አከባበርን አስመልክቶ በተዘጋጀ የገንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ሙስና ሕዝብ በመንግሥት እና በሕግ የበላይነት ላይ አመኔታ እንዲያጣ የማድረግ ጉልበት ያለው መሆኑን በመጥቀስ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በእጅጉ በማዳከምና በመጉዳት የሞራልና የሥነምግባር ቀውስ እንዲፈጠር የሚያደርገውን የሙስና ወንጀል በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የሴቶችና...

2399

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሴቶችና ሕጻናት ዙሪያ የሚኖርን የፍትሕ ተገማችነትን ለማስፋት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሥርዓተ-ችሎት እንዲዘጋጅ እያደረገ እንደሚገኝ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ አስታወቁ፡፡

ም/ፕሬዚደንቱ ይህን ያስታወቁት የፌደራል ፍ/ቤቶች ዓለም ዓቀፍ ፀረ-ጾታዊ ጥቃት ቀንን ሕዳር 30 ቀን 2014 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት አዳራሽ በፓናል ውይይት ሲከበር ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው፡፡

First7273747577798081Last