Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ኩማ መልኩ እና አቶ ሰለሞን ዘለቀ የሰበር መ/ቁ/250546

መዝገቡ ለሰበር ችሎት የቀረበዉ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የስር ፍርድ ቤት ዉሳኔ የህግ ስህተት የለዉም በማለት በመ/ቁ/ 423754 ላይ በቀን 11/09/2015ዓ.ም የሰጠዉ ትእዛዝ የህግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል በዚህ ሰበር ችሎት እንዲታረም በማለት አመልካች ባቀረቡት አቤቱታ መነሻ ነዉ፡፡

የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ በስር ፍርድ ቤት አመልካቹ ከሳሽ ሲሆን ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን የተከራከሩ ሲሆን ጉዳዩ እርሻ መሬት ይዞታ የሚመለከት ነዉ፡፡አመልካች ሃምሌ 12 ቀን 2014ዓ.ም በዲጋሉና ጢጆ ወረዳ ፍርድ ቤት ባቀረበው አቤቱታ በዲጋሉ አራቢ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘውን አዋሳኞቹ በክሱ የተጠቀሰ መሬት ከአያቴ ከበደ ዋቅጅራ እና ሴት አያቴ ወ/ሮ የሺ ተ/ማሪያም በመ/ቁ/43575 በሆነው በዉርስ ተወስኖልኝ በመ/ቁ 43575 ተፈጽሞልኝ እያለ ተጠሪ ምንም መብት ሳይኖረዉ ስለያዘብኝ እንዲለቅልኝ ሲል የጠየቀ ሲሆን ተጠሪ ጥቅምት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ባቀረበው መልስ ይዞታው የአመልካች አያቶች ሳይሆን በቅይይር ከአቶ ታደሰ ከበደ ያገኘሁት የግል ይዞታዬ ነው፤የተቀያየርነውን ይዞታ ሰዎች ተቀብለው የመኖሪያ ቤት የሰሩበት ሲሆን እኔም ይዞታውን እየተጠቀምኩበት ስለሆነ ክሱ ተቀባይነት የለዉም በማለት ተከራክሯል፡፡መልካም ንባብ…..

Previous Article እነ ወ/ሮ ጌጤ ሙለታ(3ሰዎች) እና ወ/ሮ ብርሃኔ ካባ የሰ/መ/ቁ 249367
Next Article እነ ወ/ሮ ዘውዲቱ ድንቁ(2ሰዎች)የቀድሞ አርጋፋ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት (በአሁን አርጋፋ ማዘጋጃ ቤት)የሰ/መ/ቁ፡- 250597
Print
3204

Documents to download

  • 250546(.pdf, 1.07 MB) - 373 download(s)

«February 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2627282930311
2345678
9101112131415
16171819202122
2324252627281
2345678

የኢኮቴ ተጠቃሚነትን ማሳደግ በስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ቁልፍ...

2836

በአማካሪ ድርጅት እየተዘጋጀ ያለው ሶስተኛው የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ረቂቅ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ለፍርድ ቤቶች ከፍተኛ አመራሮች በቀረበበት መድረክ የኢኮቴ ተጠቃሚነትን ማሳደግ ከቁልፍ የውጤት መስክ መካከል አንዱ እንዲሆን አስተያየት ቀረበ፡፡

የተሻሻሉት የፌደራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ እና...

4037

የተሻሻለው የፌደራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ እና የዳኝነት አስተዳደር አዋጆች በቅርቡ መጽደቃቸው የፌደራል ፍርድ ቤቶች ለጀመሩት የሪፎርም ሥራ መሠረት መሆናቸው ተገለጸ፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ይህን የገለጹት የፍርድ ቤቱ አመራሮችና ዳኞች በፌዴራል ፍርድ ቤቶች የ2013 የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ግንቦት 14 ቀን 2013 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል ሲወያዩ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡

ፍርድ ቤቱ ባቀረበው የበጀት ጥያቄ ላይ በምክር ቤቱ...

2744

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን የ2014 በጀት ዓመት የበጀት ፍላጎት ለኢፌዲሪ ሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ማቅረቡን ተከትሎ በበጀት ፍላጎት ላይ ለተነሱ ማብራሪያ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች መግለጫ ሰጠ፡፡

የተማሪዎችን የሕግ ግንዛቤ ለማሳደግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ

3360

በትምህርት ቤቶችና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች ያላቸውን የሕግ ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ በትምሕርት ሚኒስቴር፣ በሳይንስና ከፍተኛ ትምሕርት ሚኒስቴር እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መካከል ተፈረመ፡፡

First7374757677798182