Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ቴዎድሮስ መስፋን ህንፃ ሥራ ተቋራጭእና አዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት (በአሁኑ - የአ/አ ቤ/ልማት ኮርፖሬሽን) የሰበር መ/ቁ 253303

በዚህ መዝገብ የተያዘው ጉዳይ የግንባታ ዉልን የሚመለከት ነዉ፡፡ ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ አመልካች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 04664 እና መ/ቁ 06910 አጣምሮ ሰኔ 24 ቀን 2014 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ ፤ የአዲስ አበባ ከተማ ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 37544 ህዳር 28 ቀን 2015 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ ፤ እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 40218 ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ በመቃወም ነው፡፡

ተጠሪ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ባቀረበው ክስ  ከአመልካች ጋር መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ/ም ጠቅላላ ዋጋዉ የብር 19,044,907.52 (አስራ ዘጠኝ ሚሊዮን አርባ አራት ሺ ዘጠኝ መቶ ስባት ከ52/100) የህንፃ ግንባታ ዉል የፈፀምን ሲሆን መንግስት ለዜጎች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ በዘርፉ የሚገኙ ተቋራጮች በአንድ ዘርፍ ብቻ እንዲሳተፉ ስለተደረገ አመልካች በአዲስ አበባ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ሥር በግንባታ ስራ ያለመሳተፍ ማስረጃ አንዲያቀርብ ተጠይቆ ተጠሪ መስከረም 12 ቀን 2008 ዓ/ም የተፃፈ ሀሰተኛ ማስረጃ በማቅረቡ በዉሉ አንቀፅ 2 መሰረት የማጭበርበር ስራ የፈፀመ በመሆኑ ዉሉ የተቋረጠ ሲሆን አመልካች አለአግባብ የወሰደውን ብር 3,264,297.15 (ሶስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ስልሳ አራት ሺ ሁለት መቶ ዘጠና ስባት ከ15/100) ቅድመ ክፍያ ለመመለስ ፍቃደኛ ስላልሆነ ይህን ገንዘብ ከወለድ ጋር እንዲከፍል ይወሰንልኝ በማለት ክስ አቅርቧል፡፡መልካም ንባብ…..

Previous Article ደጀኔ ደበላ አልቀረበም እና ኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 251700
Next Article ሐረማያ ዩንቨርስቲ እና መላ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግል ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 253530
Print
4314

Documents to download

  • 253303(.pdf, 1.03 MB) - 516 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

በዳኝነት ስርአቱ ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን...

666

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በዳኝነት ስርአት ውስጥ ለህጻናት ተስማሚ የፍትህ ስርአትን ለማጎልበት ከአጋር ድርጅቶች ጋር የጋራ ውይይት መድረክ በቀን 03/06/2018 ዓ.ም ተካሂዷል።

ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶች ...

802

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዲስ ተሿሚ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ክቡር አቶ ልዑል ካህሳይን እና ክቡር አቶ ምትኩ ማዳን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አመራሮች እና የስራ ሃላፊዎች ጋር በቀን 02/06/2018 ዓ.ም ትውውቅ እና የስራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

በቆይታቸውም የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሪፎርም ተግባራት ላይ ገለጻ እና የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶች ላይ ማብራሪያ የቀረበላቸው ሲሆን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሚገኙ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ 2018 ዓ.ም የመጀመሪያ መንፈቅ...

1195

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2018 የመጀመሪያዉ መንፈቅ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት የውይይት መድረክ የፍርድ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳኞች እና የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተደርጓል፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል...

637

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥር 28 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደዉ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና 50 የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት አጽድቋል፡፡

First34568101112Last