Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ ተፈራ ፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽ/ቤት፤የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ 259947

ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ በማህበር በመደራጀት ከተገኘዉ ይዞታ ጋር የተያያዘ ሲሆን አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት  ክስ በ03/08/1990 ዓ/ም ተመዝግቦ በፀደቀዉ የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የተደራጀ ታቦር የመኖሪያ ቤቶች ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል በመሆን ተደራጅተዉ ማኅበሩ በሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ካገኘዉ ጠቅላላ ይዞታ ላይ መጠኑ 203.67 ካሬ ሜትር የሆነዉን የክርክሩን ይዞታ   በድርሻ እንደሰጣቸዉና የዚሁ ይዞታ ሕጋዊ ባለመብት ስለመሆናቸዉም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 281839 በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤትና በኮልፌ  ቀራኒዮ ክለ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት ላይ ክስ አቅርበዉ መብታቸዉ ተረጋግጦ ዉሳኔ እንዲያገኝ የሚል ነው፡መልካም ንባብ…

Previous Article ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243
Next Article ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና ሚኒስቴር የሰ.መ.ቁ 260594
Print
5519

Documents to download

  • 259947(.pdf, 828.26 KB) - 696 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞችና የአስተዳደር ዘርፍ ክፍል...

3387

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች እና የአስተዳደር ዘርፍ ከፍል ሃላፊዎች በሃገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ባለው “ኢትዮጵያን እናልብስ” ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በመሳተፍ የሃገራችንን የደን ሽፋን የማሳደግና የአየር ንብረትን የመጠበቅ ኃላፊነታችውን ለመወጣት በጉለሌ ዕጽዋት ማዕከል 600 ሃገር በቀል የዛፍ ችግኞችን ተክለዋል፡፡

የፌዴራል ዳኞች የጉባዔ ተወካዮቻቸውን መረጡ

3284

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ የሚወክሏቸውን 3 ዳኞች መረጡ፡፡ የቀድሞውን የዳኞች አስተዳድር ጉባዔ አዋጅ 684/2002ን ለማሻሻል የወጣው የፌዴራል ዳኝነት አስተዳደር አዋጅ 1233/2013 አስራ አምስት ዓባላት ያሉት የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ያቋቋመ ሲሆን በአዋጁ እንቀጽ 6(1/ቀ) መሰረት ከሶስቱም ፌዴራል ፍርድ ቤቶች በዳኞች ጠቅላላ ስብሰባ የተመረጡ አንድ ወንድ እና ሁለት ሴት ዳኞች በድምሩ ሶስት ዳኞች አባል እንዲሆኑ ይደነግጋል፡፡

በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተቋማዊ መዋቅር ላይ ምክክር ተካሄደ

3300

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አመራሮችና የመዋቅር ስራ ክትትልና ቁጥጥር ኮሚቴ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የህገመንግስቱ መጽደቅን ተከትሎ በያዙት አደረጃጀት ተቋማቂ ተልዕኮአቸውን ለመወጣት እንዲያስችላቸው ተግባራዊ በተደረጉ ሶስት ተቋማዊ መዋቅር ላይ ምክክር አካሄዱ፡፡

በቅርቡ የፀደቁ የፍርድ ቤቱን አዋጆች ተግባራዊ ለማድረግ...

3118

ማሻሻያ ተደርጎባቸው በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፀደቁትን የፌደራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/2013 እና የፌደራል ዳኝነት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1233/2013 ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ደንቦችና መመሪያዎች ዝግጅት እየተፋጠነ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡

First7879808183858687Last