Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተገኝ ደምሴ ወንድአፍራሽ እና ወ/ሮ አየለች ደሳለኝ እንዳሻው የሰበር መ/ቁጥር 248810

ጉዳዩ የንብረት መፋለም ክስን የሚመለከት ነው፡፡ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የሐረሪ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ/ቁ.13375 በቀን 18/11/2011 ዓ/ም የሰጠውን ውሳኔ የክልሉ  ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ችሎት በመ/ቁ. 04927 በቀን 01/04/2012 ዓ/ም የቀረበውን ይግባኝ ቅሬታ ባለመቀበል የሥር ፍርድ ቤትን ውሳኔ በትዕዛዝ በማጽናት የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል አመልካች ሰኔ 09 ቀን 2015ዓ/ም በተጻፈ አቤቱታ ቅሬታ በማቅረባቸው ነው፡፡

 ከሥር ፍርድ ቤቶች የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው በሥር ፍርድ ቤት አመልካች ተከሳሽ  ተጠሪ ከሳሽ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ በ23/03/2008ዓ/ም ጽፈው ባቀረቡት ክስ አዋሳኞቹ በክሱ የተጠቀሰው የቤት ቁጥር 144 የሆነ በ 2921 ካ.ሜ የመሬት ይዞታ ላይ ያረፈ ሰባት ክፍሎች ያሉት ፎቅ ቤትና ሰርቪስ ቤት ሟች እህታችን በግዥ አግኝተው ሲጠቀሙበት ቆይተው በ1962 ዓ/ም በነበረው የሶማሊያ ጦርነት ወጥተው ስላልተመለሱ ተጠሪ ከወንድሜ ሻምቤል ፈለቀ ደሳለኝ ጋር በመሆን የእህታችንን መጥፋት እና ወራሽነት በ1972 ዓ/ም አሳውጀውን ቤቱ በውርስ ለተጠሪ እና ወንድሜ ከተላለፈ በኃላ፤ የተጠሪ ወንድም በ1988 ዓ/ም በውርስ ያገኙትን የአከራካሪውን ቤት ድርሻ በስጦታ ያስተላለፉልኝን ጨምሮ ከጠቅላላ ይዞታ ውስጥ በ1394 ካ/ሜ ላይ ካርታ በስሜ 11/09/1996 ዓ/ም የተሰራልኝ ሲሆን ቀሪው 1527 ካ/ሜ ይዞታ እና ፎቅ ቤት ወደ ፊት ይሰራልሻል ተብዬ ነበር፤ከዚያ በኋላ ሟች እህቴ ያከራየቻቸው የተከሳሽ ቤተሰቦችከ1969 ዓ/ም ጀምሮ በቤት ውስጥ መኖር ቀጠሉ፤ አመልካች ምንም መብት ሳይኖረው በምዕራብ አቅጣጫ የሚገኙትን አምስት ክፍል ቤቶችን ይዞ በማከራየት፤ ከ2001 ዓ/ም እስከ 2004 ዓ/ም ተለጣፊ ቤቶችን በመስራት እየተጠቀሙ በመሆኑና ቤቱንም ለማስረከብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ በሕገ-ወጥ መንገድ የሠሩትን ቤት አፍርሰው የቤት ቁጥር 144 እና ይዞታውን ለቀው እንዲያስረክቡ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…

Previous Article ቁአቶ ጌታቸው ጎነሞ እና አቶ ፍሰሀ ታምራትየሰ/መ/ቁ249348
Next Article የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገቢዎች ቢሮ ዓቃቤ ሀግ እና ወ/ሮ መዓዛ በልስቲየሠ/መ/ቁጥር 248735
Print
4931

Documents to download

  • 248810(.pdf, 854.77 KB) - 624 download(s)

«July 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
293012345
6789101112
13141516171819
20212223242526
272829303112
3456789

በፍትሃ ብሔር ፍርደ አፋጻጸም በሚታዩ ተግዳሮቶች እና...

3190

ሰኔ 6 ቀን 2013 ዓ.ም/ ቢሸፍቱ/ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በፍትሃ ብሔር ጉዳዮች ላይ የሚሰጧቸውን ውሳኔዎችና ትእዛዞችን በማስፈጸም ሂደት በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችና ሊወሰዱ በሚገቡ የማስትካከያ እርምጃዎች ላይ ከባልድርሻ እካላት ጋር ምክክር አደረገ።

በረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የአስተዳደር ሰራተኞች...

3676

በረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የአስተዳደር ሰራተኞች ግብአት የሚሰጡበት ሁኔታ መመቻቸቱ  ሰራተኞች በፍርድ ቤቶች የማሻሻያ ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ እንዲሚያሰፋው ተገለጸ፡፡

 

ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች የተውጣጡ የአስተዳደር ሰራተኞች በአማካሪ ድርጅቱ በመዘጋጀት ላይ ባለው ረቂቅ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ተጨማሪ ግብአት እንዲሰጡ ሁኔታዎች መመቻቸታቸው የአስተደደር ሰራተኞች በፍርድ ቤቶች በመተግበር ላይ ባለው የማሻሻያ ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ እንደሚያሰፋ ገለጹ፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የአስተዳደር ሠራተኞች ረቂቅ...

4583

የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መጽደቁን ተከትሎ በፍርድ ቤቶች ከዳኞች ውጭ ያሉ የአስተዳር ሠራተኞች የሚተዳደሩበት ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ላይ የግብአት ማሰባሰቢያ ውይይት ተካሔደ፡፡

ለ68 ዓመታት በሥራ ላይ የቆየውን የዳኝነት ክፍያ...

3810

ከ1945 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የቆየውን የፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያ እና የአከፋፈል ሥርዓት ለማሻሻል ተዘጋጅቶ በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ግንቦት 21 ቀን 2013 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል የግማሽ ቀን ውይይት ተካሔደ፡፡

First8081828385878889