Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ተገኝ ደምሴ ወንድአፍራሽ እና ወ/ሮ አየለች ደሳለኝ እንዳሻው የሰበር መ/ቁጥር 248810

ጉዳዩ የንብረት መፋለም ክስን የሚመለከት ነው፡፡ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የሐረሪ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ/ቁ.13375 በቀን 18/11/2011 ዓ/ም የሰጠውን ውሳኔ የክልሉ  ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ችሎት በመ/ቁ. 04927 በቀን 01/04/2012 ዓ/ም የቀረበውን ይግባኝ ቅሬታ ባለመቀበል የሥር ፍርድ ቤትን ውሳኔ በትዕዛዝ በማጽናት የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል አመልካች ሰኔ 09 ቀን 2015ዓ/ም በተጻፈ አቤቱታ ቅሬታ በማቅረባቸው ነው፡፡

 ከሥር ፍርድ ቤቶች የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው በሥር ፍርድ ቤት አመልካች ተከሳሽ  ተጠሪ ከሳሽ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ በ23/03/2008ዓ/ም ጽፈው ባቀረቡት ክስ አዋሳኞቹ በክሱ የተጠቀሰው የቤት ቁጥር 144 የሆነ በ 2921 ካ.ሜ የመሬት ይዞታ ላይ ያረፈ ሰባት ክፍሎች ያሉት ፎቅ ቤትና ሰርቪስ ቤት ሟች እህታችን በግዥ አግኝተው ሲጠቀሙበት ቆይተው በ1962 ዓ/ም በነበረው የሶማሊያ ጦርነት ወጥተው ስላልተመለሱ ተጠሪ ከወንድሜ ሻምቤል ፈለቀ ደሳለኝ ጋር በመሆን የእህታችንን መጥፋት እና ወራሽነት በ1972 ዓ/ም አሳውጀውን ቤቱ በውርስ ለተጠሪ እና ወንድሜ ከተላለፈ በኃላ፤ የተጠሪ ወንድም በ1988 ዓ/ም በውርስ ያገኙትን የአከራካሪውን ቤት ድርሻ በስጦታ ያስተላለፉልኝን ጨምሮ ከጠቅላላ ይዞታ ውስጥ በ1394 ካ/ሜ ላይ ካርታ በስሜ 11/09/1996 ዓ/ም የተሰራልኝ ሲሆን ቀሪው 1527 ካ/ሜ ይዞታ እና ፎቅ ቤት ወደ ፊት ይሰራልሻል ተብዬ ነበር፤ከዚያ በኋላ ሟች እህቴ ያከራየቻቸው የተከሳሽ ቤተሰቦችከ1969 ዓ/ም ጀምሮ በቤት ውስጥ መኖር ቀጠሉ፤ አመልካች ምንም መብት ሳይኖረው በምዕራብ አቅጣጫ የሚገኙትን አምስት ክፍል ቤቶችን ይዞ በማከራየት፤ ከ2001 ዓ/ም እስከ 2004 ዓ/ም ተለጣፊ ቤቶችን በመስራት እየተጠቀሙ በመሆኑና ቤቱንም ለማስረከብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ በሕገ-ወጥ መንገድ የሠሩትን ቤት አፍርሰው የቤት ቁጥር 144 እና ይዞታውን ለቀው እንዲያስረክቡ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…

Previous Article ቁአቶ ጌታቸው ጎነሞ እና አቶ ፍሰሀ ታምራትየሰ/መ/ቁ249348
Next Article የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገቢዎች ቢሮ ዓቃቤ ሀግ እና ወ/ሮ መዓዛ በልስቲየሠ/መ/ቁጥር 248735
Print
4395

Documents to download

  • 248810(.pdf, 854.77 KB) - 570 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሀዋሳ ማዕከል በይፋ...

6031

የፌዴራል ጉዳዮችን በውክልና እንዳይመለከቱ ስልጣናቸው በተነሳባቸው የክልል ፍርድ ቤቶች የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተዘዋዋሪ ችሎት በማደራጀት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

የአዋጅ መሻሻልን ተከትሎ በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት...

3639

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 25/88 እና ሌሎች ተከታታይ የአዋጁ ማሻሻያዎችን በመሻር በጥር ወር 2013 ዓ.ም  በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የጸደቀው አዲስ አዋጅ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍትሐ ብሔር ስረ-ነገር ሥልጣን ላይ ለውጥ ማድረጉን ተከትሎ በፌዴራል መጀመሪያ ድረጃ ፍርድ ቤት ሊኖር ስለሚችል የችሎት አደረጃጀት እና የዳኞች አሰያየምን ለማመላከት የተካሄደ የዳሰሳ ጥናት ውጤት ሚያዚያ 15 ቀን 2013 ዓ.ም ለፍ/ቤቱ አስተባባሪ ዳኞች፤ ዳኞች፣ ለሬጂስትራሮችና ለልዩ ልዩ የስራ ክፍል ኃላፊዎች ለአስተያየት ቀረበ፡፡

የፌዴራል ፍ/ቤቶች ከፍተኛ አመራር እንዲያጸድቅ በቀረቡለት...

3616

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶችና ም/ፕዝደንቶች ሚያዚያ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ እንዲያጸድቃቸው በቀረቡለት የፍትሃብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር ረቂቅ መመሪያ እና የተሸሻለውን የCCMS (Court Case Management System) ለመተግበር የሚያስችል የስራ መዘርዝር እና ፍሰት የሚገልጽ ሰነድ ላይ ተወያየ፡፡

First8081828384858789