Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

አቶ ቴዎድሮስ መስፋን ህንፃ ሥራ ተቋራጭእና አዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት (በአሁኑ - የአ/አ ቤ/ልማት ኮርፖሬሽን) የሰበር መ/ቁ 253303

በዚህ መዝገብ የተያዘው ጉዳይ የግንባታ ዉልን የሚመለከት ነዉ፡፡ ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ አመልካች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 04664 እና መ/ቁ 06910 አጣምሮ ሰኔ 24 ቀን 2014 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ ፤ የአዲስ አበባ ከተማ ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 37544 ህዳር 28 ቀን 2015 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ ፤ እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 40218 ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ በመቃወም ነው፡፡

ተጠሪ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ባቀረበው ክስ  ከአመልካች ጋር መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ/ም ጠቅላላ ዋጋዉ የብር 19,044,907.52 (አስራ ዘጠኝ ሚሊዮን አርባ አራት ሺ ዘጠኝ መቶ ስባት ከ52/100) የህንፃ ግንባታ ዉል የፈፀምን ሲሆን መንግስት ለዜጎች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ በዘርፉ የሚገኙ ተቋራጮች በአንድ ዘርፍ ብቻ እንዲሳተፉ ስለተደረገ አመልካች በአዲስ አበባ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ሥር በግንባታ ስራ ያለመሳተፍ ማስረጃ አንዲያቀርብ ተጠይቆ ተጠሪ መስከረም 12 ቀን 2008 ዓ/ም የተፃፈ ሀሰተኛ ማስረጃ በማቅረቡ በዉሉ አንቀፅ 2 መሰረት የማጭበርበር ስራ የፈፀመ በመሆኑ ዉሉ የተቋረጠ ሲሆን አመልካች አለአግባብ የወሰደውን ብር 3,264,297.15 (ሶስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ስልሳ አራት ሺ ሁለት መቶ ዘጠና ስባት ከ15/100) ቅድመ ክፍያ ለመመለስ ፍቃደኛ ስላልሆነ ይህን ገንዘብ ከወለድ ጋር እንዲከፍል ይወሰንልኝ በማለት ክስ አቅርቧል፡፡መልካም ንባብ…..

Previous Article ደጀኔ ደበላ አልቀረበም እና ኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 251700
Next Article ሐረማያ ዩንቨርስቲ እና መላ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግል ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 253530
Print
4314

Documents to download

  • 253303(.pdf, 1.03 MB) - 516 download(s)

«June 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
25262728293031
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293012345

የፌደራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የ2018...

957

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤትና መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት 2018 በጀት ዓመት የመንፈቅ አመት አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ በቀን 27/2018 ዓ.ም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት፣ የሶስቱም ፍርድ ቤቶች አመራሮችና የማኔጅመንት ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

የፌዴራል መንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር አዋጅ...

928

ከመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ጋር በመተባበር በመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር አዋጅ 1333/2016፣ መመሪያዎች እና ኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥ አጻጸም (e-GP) ስርዓት ክህሎት ላይ ከጥር 21 እስከ 23/2018 ዓ.ም ለሦስት ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል ፡፡

ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሬጂስራርና ችሎት አገልግሎት...

597

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሬጂስትራርና ችሎት አገልግሎት ክፍል ለተውጣጡ ሰራተኞች በሙስና ምንነት፣ በሙስና ባህሪያት፣ በአዋጅ 881/2007 የተደነገጉ የሙስና ወንጀሎች፣ የሙስና መከላከያ ስልቶች እና በሥነ ምግባር ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ በቀን 23/5/2018 ዓ.ም ስልጠና ተሰጥቷል::

የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር አመራሮች በፌደራል...

591

የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር አመራሮች በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 20/05/2018 ዓ.ም በመገኘት ወደፊት በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡

First45679111213Last