በአገራችን ፍርድ ቤቶች የቅጣት ውሳኔዎችን ወጥነት እና ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የቅጣት አወሳሰን መመሪያ መኖር አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህንኑ መመሪያ የማውጣት ሥልጣን በወንጀል ሕግ አንቀጽ 88(4) በተሰጠው መሠረት ፍርድ ቤቱ በቅርቡ አሻሽሎ ባወጣው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 ላይ ለፌደራልና ለክልል የፍትሕ ተቋማት ተሳታፊዎች ከሐምሌ 10-12 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሰጥ የቆየው የአሰልጣኞች ሥልጠና ተጠናቀቀ፡፡