Selam Warga
/ Categories: CASSATION, Cassation

ወ/ሮ ፋንቱ ዘነበ (2ሰዎች) እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የእንጦጦ ስብሐት ቅድስት ስላሴ ቤተ-ክርስቲያን መ.ቁ 246386

የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተጠሪ ከሳሽ በመሆን አመልካቾች 1ኛ እና 4ኛ ተከሳሽ በመሆን እንዲሁም በዚህ ክርክር ተካፋይ ያልሆኑት እነ ሳልሳይ ኤፍሬም ጌታቸው 4 ሰዎች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ፣ 3ኛ፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች በመሆን ተከራክረዋል፡፡ተጠሪ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረበችው የተሻሻለ ክስ የአባ ኃይለስላሴ መገኖ ርስት እና ንብረት የሆነው አንድ ጋሻ ይዞታ ሰኔ 17 ቀን 1948 ዓ.ም በተደረገ ግልጽ ኑዛዜ የተሰጣት መሆኑን ኑዛዜው በከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 169/55 ግንቦት 13 ቀን 1955 ዓ.ም መጽደቁን እና ከሳሽ ይዞታውን ተረክባ ስታስተዳድር የቆየች መሆኑን፤ ከአንድ ጋሻ መሬት ላይ 1192 ካ.ሜ ይዞታ ቀንሳ ለአገልጋይ ካህናት ደመወዝ መክፈያ ይሆን ዘንድ የ1ኛ አመልካች ባለቤት ለነበሩት ለአቶ ኤፍሬም ጌታነህ በወር ብር 30 (ሰላሳ) ሂሳብ ለአምስት ዓመታት አከራይታ የኪራይ ውሉ እስከ 1967 ዓ.ም እየተራዘመ መቆየቱን፤ ይዞታው ያልተወረሰ እና የግል ቤቴ ነው በማለት አቶ ኤፍሬም ጌታነህ በ2004 ዓ.ም ባቀረቡት አቤቱታ መነሻ እንደ ቅደም ተከተላቸው የስር 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች የነበሩት ጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 01 አስተዳደር እና ጉለሌ ክ/ከተማ መሬት አስተዳደር የቤት ቁጥር 815(ለ) በሚል በአቶ ኤፍሬም ጌታነህ ስም ተመዝግቦ ስም እንዲዞር ማድረጋቸውን፤ ይህንኑ ይዞታ የአቶ ኤፍሬም ጌታነህ ወኪልና የስር 4ኛ ተከሳሽ(2ኛ አመልካች) የቦርድ ሰብሳቢ በሆኑት አቶ መኮንን አያሌው እና የተጠሪ ፀሀፊ ዲያቆን ተስፋሚካኤል ታደሰ አመልካችነት ይዞታው ወደ አቶ ኤፍሬም ጌታነህ እንዲተላለፍ በመጠየቁ ህዳር 17 ቀን 2005ዓ.ም ቁጥሩ 22/69/28322/00 የሆነ ካርታ በአቶ ኤፍሬም ጌታነህ ስም ተዘጋጅቶ ተሰጥቷል፡፡ ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም በተደረገ በሽያጭ ውል ለ2ኛ አመልካች(ስር 4ኛ ተከሳሽ) ተላልፏል፡፡ የተጠሪ ይዞታ ከህግ ውጪ የተላለፈ በመሆኑ የስር 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች የይዞታውን ባለቤት በአግባቡ ሳያጣሩ በአቶ ኤፍሬም ጌታነህ ስም በ17/3/2005ዓ.ም አዘጋጅተው የሰጡትን ካርታ እንዲሰርዙ፤ በሟች አቶ ኤፍሬም ጌታነህ እና በስር 4ኛ ተከሳሽ(2ኛ አመልካች) መካከል የተደረገው በ15/12/2005ዓ.ም የተደረገው ውል እንዲሰረዝ፤ የስር 5ኛ ተከሳሽ አለአግባብ በሰጠው መረጃ መሰረት ለስር 4ኛ ተከሳሽ(2ኛ አመልካች) የተሰጠው ካርታ እንዲሰረዝ፤ በምትኩ የስር 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች ለይዞታው ለተጠሪ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲሰጡ፤ በይዞታው ላይ ያለን ንብረት 2ኛ አመልካች አንስቶ ይዞታውን ለተጠሪ እንዲያስረክብ እንዲወሰን በማለት ዳኝነት ጠይቃለች፡፡ ማስረጃዎችንም አያይዛለች፡፡ነው፡፡መልካም ንባብ…

Previous Article ሲቀላ ክፍለ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና ወ/ሮ አረግዋ ጠብቀው የሰበር መዝገብ ቁጥር - 247036
Next Article ቢትወደድ ጂማ እና እነ አቶ ሳምሶን መለሰ (2ሰዎች)የሰበር መዝገብ ቁጥር - 245370
Print
4830

Documents to download

  • 246386(.pdf, 896.3 KB) - 641 download(s)

«August 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
31123456

‎በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአርባ ምንጭ ማዕከል...

4

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአርባ ምንጭ ማዕከል የተዘረጉትን የኢ-ፋይሊንግ፣ የትራንስክሪፕሽን እና የርቀት ችሎት አገልግሎቶችን በአካል ተገኝተው አስመርቀዋል።

የፍርድ ቤቶች አመራሮችና ዳኞች በአርባምንጭ ከተማ የችግኝ...

0

ነሐሴ 03/2018 ዓ.ም (የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት)
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የተመራ የፍርድ ቤቶች ከፍተኛ አመራሮችና ዳኞች ልዑክ በአርባምንጭ ከተማ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል።

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጉባኤ ተካሄደ

11

ፌደራል ፍርድ ቤቶች ጉባኤ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

‎የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትና የጉባኤው ሰብሳቢ ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በመክፈቻ ንግግራቸው፤ በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሠረት የተቋቋመው የፌደራል ጉባኤ የዳኝነት ነፃነትና ገለልተኝነትን የመጠበቅ፣ የአሰራር መመሪያዎችን የማውጣትና የማሻሻል እንዲሁም አገራዊ የዳኝነት ሂደቱን የማጠናከር ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለበት ገልጸዋል።

12345678910Last