ከፌደራል ፍርድ ቤቶች፣ ከፍትሕ ሚኒስቴር፣ ከፌደራልና ከአዲስ አበባ ፖሊስ፣ ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር እና ከፌደራል ጠበቆች ማሕበር የተወከሉ የሥራ ኃላፊዎች፣ ዳኞች እንዲሁም ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በተከታታይ የወንጀል ክስ አሰማም ሂደት (Continuous Criminal Trial) ላይ ‹‹Assessment of gaps that obstruct continuous ctriminal trials in federal courts›› በሚል ርዕስ በተከናወነ ጥናት ላይ የማረጋገጫ እና የምክክር መድረክ (Validation Workshop) ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሄዷል፡፡