የፌደራል ፍርድ ቤቶች በነሐሴ እና መስከረም ወራት በከፊል ዝግ ሆነው መቆየታቸውን ተከትሎ የ2016 በጀት ዓመት መደበኛ የዳኝነት አገልግሎት ለማስጀመር ጥቅምት 1 ቀን 2016 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተዘጋጀ ሥነ ሥርዓት ተካሔደ፡፡ መደበኛ የዳኝነት አገልግሎት ለማስጀመር የተካሔደውን ሥነ ሥርዓት ተከትሎ የፌደራል ፍርድ ቤቶች መደበኛ የዳኝነት አገልግሎታቸውን በይፋ ጀምረዋል፡፡
በስነ-ስርዓቱ ላይ የሶስቱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶችና ምክትል ፕሬዝደንቶች እንዲሁም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችን ጨምሮ የስራ ክፍል ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ታዳሚ ሆነዋል፡፡