የሰበር ውሳኔዎች

 

ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ...

የአሁን አመልካች በምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ/መ/ቁ 47863 እና በመ/ቁ በመ/ቁ 47862 በሁለቱም መዝገቦች ላይ 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው የክስ ይዘትም አመልካች የኢትዮጵያ የፌዴራል ቡና... Read more

አቶ መሀመድ አለሙ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ...

ጉዳዩ የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ አሁን የክርክሩ አካል ያልሆነው የትኦትኦ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ 2ኛ ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ በስር ፍርድ... Read more

ወ/ሮ በላይነሽ ኩምሳ እና ግብርና...

የጉዳዩ አመጣጥ ተጠሪ ለአመልካች በቁጥር ማዕ/ሠ831በ/1/2 በ4/11/2015ዓ.ም በተጻፈ በቁጥር ማዕ/ሠ831በ/1/1 በ9/10/2015 በተጻፈ የምደባ ደብዳቤ ላይ የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ውስጥ በደረጃ XVIII በመደብ... Read more

አቶ ተስፋዬ ደገፋ እና ዶ/ር ትዕዛዙ...

ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን በከፍተኛዉ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን መከራከራቸዉን የሥር ፍ/ቤቶች ዉሳኔ ያመለክታል፡፡ ክርክሩ... Read more
12345678910Last
«July 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
30123456
78910111213
14151617181920
21222324252627
28293031123
45678910

ፍርድ ቤቱ ለአራት ክልሎች ጠቅላይ ፍ/ቤቶች የቁሳቁስ...

1089

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አራት የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2014 ዓ.ም የሰባት ሚሊዮን ብር ግምት ያለው የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡

የቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው ለአማራ እና ለአፋር ክልሎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች እንዲሁም በቅርቡ በአዲስ መልክ በክልልነት የተቋቋሙትን የሲዳማ እና የደቡብ ምዕራብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር ነው፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት...

1035

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የተወሰዱ እርምጃዎች

የካቲት 6 ቀን 2014 ዓ.ም «የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ» ዓመታዊ ጉባኤ ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ባቀረቡት ሪፖርት በ2013-2014 በጀት ዓመት አጋማሽ በፍርድ ቤቱ የሪፎርም ሥራዎች ዙሪያ የተከናወኑ ተግባራትን ዳስሰዋል፡፡ ክብርት ፕሬዚደንትዋ ዛሬም ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል ባይባልም የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የተለያዩ እርምጃዎች የተወሰዱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ይህ የገለልተኝነት እና የነጻነት ጉዳይ ዳኞች ከውጭም ሆነ ከውስጥ ጣልቃ ገብነት ተጽዕኖ ሳይደርስባቸው ሕግን ብቻ ተከትለው ውሳኔ እንዲሰጡ አስፈላጊ ሁኔታዎችን ማመቻቸትን ይጠይቅ ነበር ብለዋል፡፡ የዳኝነት ነጻነት የዳኞች ነጻነት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ፍ/ቤቱም እንደተቋም ለማንኛውም የፖለቲካም ሆነ ማህበራዊ ጫናዎች የተጋለጠ እንዳይሆን አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እና እርምጃዎችንም መውሰድ ይጠይቅ እንደነበር ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡ እንደተከናወኑ ከጠቀሷቸው ተግባራት መካከል፡-

«የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ እና የወደፊት...

1485

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ «የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ እና የወደፊት ዕይታ /State of the Judiciary/» በሚል ርዕስ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀ ጉባዔ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ የካቲት 6 ቀን 2014 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

የመጀመሪያው ጉባዔ በ2012 የተካሔደ ሲሆን መድረኩ በኮቪድ 19 ምክንያት ተቋርጦ ከቆየ በኋላ ሁለተኛው ጉባዔ በፌደራል ፍርድ ቤቶች በ2013 በጀት ዓመት እና በ2014 ግማሽ በጀት ዓመት በተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ተከናውኗል፡፡

የቅድመ መዋቅር ነባራዊ ሁኔታ ትንተና  እና ረቂቅ ተቋማዊ...

1240

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተቋማዊ መዋቅርን እንዲሰራ በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት - በፍትህ ፕሮጀክት የተቀጠረ እማካሪ ድርጅት ያካሄደውን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ነባራዊ ሁኔት ትንተና ውጤት በፍርድ ቤቱ በኩል ስራውን እንዲከታተል ለተቋቋመ አብይ ኮሚቴ አቀረበ።

አማካሪ ድርጅቱ ( HST) ቀደም ሲል እያካሄደ ያለውን ጥናት በተደጋጋሚ ለዐብይ ኮሚቴው በማቅረብና የጥናት ስልት፣ ሂደት፣ ይዘት እና ወስን ላይ የማዳበሪያ እና አቅጣጫ ጠቋሚ ሃሳቦችን ሰብስቧል።

First4647484951535455Last