የሰበር ውሳኔዎች

 

ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና...

የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ... Read more

ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና...

የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ... Read more

ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ...

ይህ የስራ ስንብት ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁን አመልካች የሥር ከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር፡፡ ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ አመልካች የፌዴራል ከፍተኛ... Read more

እነ አቢብ አብዲ (3) ሰዎች እነ ዓሊ...

ክስ ይዘት በአጭሩ: - ለ60 ዓመት በይዞታቸዉ ስር አድርገዉ ጫት በመትል፤ ቦቆሎና ማሽላ እየዘሩ ሲጠቀሙበት ነበረዉን በጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 20 ዉስጥ የሚገኘዉን ስፋቱ 60 ቆጢ የእርሻ መሬት ይዞታቸዉን በኃይል ወረራ... Read more
1345678910Last
«June 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
2627282930311
2345678
9101112131415
16171819202122
23242526272829
30123456

ፍርድ ቤቱ በስትራቴጂያዊ እና ዓመታዊ ዕቅዱ ላይ ለምክር...

1339

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ ፍትህና የዲሞክራሲ ጉዳዩች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ፍርድ ቤቱ ባዘጋጀው ሶስተኛው ስትራቴጂያዊ ዕቅድ እና ዓመታዊ ዕቅድ ላይ ማብራሪያ ሰጠ፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ በፍርድ ቤቱ በኩል ዕቅዶቹን አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያ ከመቅረቡ በፊት በሰጡት አጭር ገለጻ የዳኝነት ዘርፉ በአማካሪ ድርጅት በመታገዝ ስትራቴጂያዊ ዕቅዱን ማዘጋጀቱን፤ የዕቅዱን ይዘትና አዘገጃጀት ሂደት የሚከታተል በየደረጃ ያሉ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ የስራ ክፍል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች አባል የሆኑባቸው ዓቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ መቋቋማቸውን፤ በረቂቅ ዕቅዱ ላይ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማህበረሰብ እና ባለድርሻ አካላት መወያየታቸውን እና የተገኙ ተጨማሪ ግብዓቶችን በማካተት ተዘጋጅቶ የጸደቀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሙስና ወንጀልን በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል...

1264

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጃ ታደሰ የሙስና ወንጀልን በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል እንደሚገባ ገለጹ፡፡

አቶ ቦጃ ታደሰ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዓል አከባበርን አስመልክቶ በተዘጋጀ የገንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ሙስና ሕዝብ በመንግሥት እና በሕግ የበላይነት ላይ አመኔታ እንዲያጣ የማድረግ ጉልበት ያለው መሆኑን በመጥቀስ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በእጅጉ በማዳከምና በመጉዳት የሞራልና የሥነምግባር ቀውስ እንዲፈጠር የሚያደርገውን የሙስና ወንጀል በትብብርና በአንድነት መንፈስ መከላከል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የሴቶችና...

931

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሴቶችና ሕጻናት ዙሪያ የሚኖርን የፍትሕ ተገማችነትን ለማስፋት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሥርዓተ-ችሎት እንዲዘጋጅ እያደረገ እንደሚገኝ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ አስታወቁ፡፡

ም/ፕሬዚደንቱ ይህን ያስታወቁት የፌደራል ፍ/ቤቶች ዓለም ዓቀፍ ፀረ-ጾታዊ ጥቃት ቀንን ሕዳር 30 ቀን 2014 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት አዳራሽ በፓናል ውይይት ሲከበር ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው፡፡

የክብርት ፕሬዝደንቷ ጉብኝት በድሬደዋ ምድብ ችሎቶች

1351

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የፌዴራል ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ድሬደዋ ምድብ ችሎቶችን ጎብኝተዋል::

ክብርት ፕሬዝደንቷ በጉብኝታቸው ከሁለቱም ፍርድ ቤቶች ምድብ ችሎቶች የዳኝነት አገልግሎት የሚሰጥበትን ሁኔታ እና የምድብ ችሎቶቹን የችሎት እና የልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎችን አደረጃጀት ተመልክተዋል፡፡ ከፍርድ ቤቶቹ ክቡራን ዳኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች ጋርም ወይይት አካሄደዋል::

First4849505153555657Last