1981
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሐሙስ መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በአራት ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ሶስት ጉዳዮች ላይ ለውሳኔ አሰጣጥ እንዲያመች ተጠሪዎች መልስ እንዲሰጡበት አቅጣጫ ሲያስቀምጥ በአንድ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ መረጃዎች ተጣርተው እንዲቀርቡ ትእዛዝ በማስተላለፍ በይደር አሳልፎታል፡፡
1943
መጋቢት 27ቀን 2015 ዓ.ም፡- የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዲስ በተሾሙ ፕሬዝዳንቶች እና በቀድሞ ፕሬዝዳንቶች መካከል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳነት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምሕረት (ረዳት ፕሮፌሰር) በተገኙበት የስራ ርክክብ ስነስረዓት ተፈጸመ፡፡
1509
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ ቴሌኮም ጋር የተፈራረመው የመግባቢያ ስምምነት (Memorandum of Understanding) በዳኝነት አገልግሎት አሠጣጥ ዘርፍ የተሰማሩ የፍርድ ቤቱን ዳኞችና ሌሎች ባለሙያዎች ጫና ለመቀነስና የፍ/ቤቱን አገልግሎት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ገለጹ፡፡
1685
የፍርድ ቤት ተገልጋዮችን ጊዜ፣ ጉልበት እና የገንዘብ ወጪ የሚቀንሱ እና የፍትሕ እርካታ የሚጨምሩ የማሻሻያ ሥራዎች የሚከናወኑ መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ገለጹ፡፡