የሰበር ውሳኔዎች

 

ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት...

በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ  የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ ትርጉም... Read more

ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት...

ከ2002 ዓ.ም እስከ 2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔዎችን ያጠቃለለ መጽሐፍ በልዮ ዕትም ለንባብ ምቹ ሆኖ ቀርቧል። Read more

ወ/ሮ የማርውሃ ወርቅነህ እና እነ ወ/ሮ...

የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች ከሳሽ አመልካች ደግሞ ጣልቃ ገብ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪዎች በቀን 11/09/2013 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ የእናታቸው ወ/ሮ ሸዋነሽ ስመኝ... Read more

ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ...

የአሁን አመልካች በምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ/መ/ቁ 47863 እና በመ/ቁ በመ/ቁ 47862 በሁለቱም መዝገቦች ላይ 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው የክስ ይዘትም አመልካች የኢትዮጵያ የፌዴራል ቡና... Read more
1345678910Last
«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ግዥን በዕውቀት ሊመሩት...

1518

የግዥን ጉዳይ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በዕውቀት ሊመሩት ይገባል ሲሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ገለፁ፡፡

በመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አዘጋጅነት ለዳኝነት አካላት በአርባ ምንጭ ከተማ ሲሰጥ በነበረው ስልጠና ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ምክትል ፕሬዝዳንቱ በአብዛኛው በከፍተኛ አመራሮች ላይ የሚቀርቡ የሙስና ወንጀል ክሶች ከግዥ ጋር የተያያዙ በመሆናቸው ከፍተኛ አመራሮች ግዥን በዕውቀት ሊመሩት ይገባል ብለዋል፡፡

 

የሌሎችን  የሥነምግባር ችግር ከሚዳኘው የዳኝነት ተቋም...

1351

ሕብረተሰቡ ከዳኞች የሚጠብቀውን የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት መጀመሪያ ዳኞች በላቀ የሥነምግባር ደረጃ ላይ ሊገኙ እንደሚገባ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ብርሐነመስቀል ዋጋሪ ገለጹ፡፡

ከፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች በፌዴራል ዳኞች ሥነምግባርና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ላይ ለሁለተኛ ዙር በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከመስከረም 14-15 ቀን 2014 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው ቲኬ ኢንተርናሽናል ሆቴል ተሰጥቷል፡፡

ክቡር ፕሬዚደንቱ በግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በፍርድ ቤቶች ከትናንት ይልቅ ዛሬ የዳኝነት ነጻነትና ተጠያቂነት አተገባበር እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቁመው ይህንም በፍ/ቤቶች ረዘም ያለ ቆይታ ያላቸው ዳኞች የሚገነዘቡት ነው ብለዋል፡፡

የፍርድ ቤቱ ሠራተኞች ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀንን አከበሩ

1376

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ23ኛ ጊዜ በመከበር ላይ የሚገኘው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ “በትዉልድ ቅብብሎሽ ኢትዮጵያ ትፀናለች” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኝ ሲሆን ቀኑ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሠራተኞች ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ/ም በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ፡፡

በዓሉ በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ሲከበር የፍርድ ቤቱ ሴቶችና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ወርቅነሽ በቀለ ባደረጉት የመክፈቻ ላይ ንግግር እንደገለጹት ከሰባት ቢሊዮን በላይ ከሚገመተዉ የዓለም ህዝብ መካከል የወጣቱ ቁጥር 1.8 ቢሊዮን እንደሚደርስና ከዚህ ውስጥ 90 ከመቶ የሚሆነዉ ወጣት በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት እንደሚገኝ ጠቅሰው ከሀገራችን የህዝብ ብዛትም 31.8 በመቶ ያህሉ ከፍተኛ አቅም ያለዉ አምራች ኃይል የሆነዉ የወጣቱ ክፍል መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ዳኞች በማያቋርጥ ሒደት ብቃታቸውን ሊያሳድጉና በሥልጠና...

1348

ዳኞች በማያቋርጥ ሒደት ብቃታቸውን ሊያሳድጉና በሥልጠና ሊያልፉ እንደሚገባ ተጠቆመ።

ዳኞች በማያቋርጥ ሒደት ብቃታቸውን ሊያሳድጉና በሥልጠና ሊያልፉ እንደሚገባ ይህም የዳኝነት ነጻነትን ለማስጠበቅና ክህሎታቸውን ለማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ም/ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ተþሊት ይመስል ገለጹ፡፡

ከፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ ከፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት እና ከፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የተውጣጡ 350 ያህል የፌደራል ፍ/ቤቶች ዳኞች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከነሐሴ 21-22 ቀን 2014 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ተካሒዷል፡፡

First4950515254565758Last