ሕብረተሰቡ ከዳኞች የሚጠብቀውን የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት መጀመሪያ ዳኞች በላቀ የሥነምግባር ደረጃ ላይ ሊገኙ እንደሚገባ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ብርሐነመስቀል ዋጋሪ ገለጹ፡፡
ከፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች በፌዴራል ዳኞች ሥነምግባርና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ላይ ለሁለተኛ ዙር በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከመስከረም 14-15 ቀን 2014 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው ቲኬ ኢንተርናሽናል ሆቴል ተሰጥቷል፡፡
ክቡር ፕሬዚደንቱ በግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በፍርድ ቤቶች ከትናንት ይልቅ ዛሬ የዳኝነት ነጻነትና ተጠያቂነት አተገባበር እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቁመው ይህንም በፍ/ቤቶች ረዘም ያለ ቆይታ ያላቸው ዳኞች የሚገነዘቡት ነው ብለዋል፡፡