የሰበር ውሳኔዎች

 

ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት...

በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ  የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ ትርጉም... Read more

ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት...

ከ2002 ዓ.ም እስከ 2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔዎችን ያጠቃለለ መጽሐፍ በልዮ ዕትም ለንባብ ምቹ ሆኖ ቀርቧል። Read more

ወ/ሮ የማርውሃ ወርቅነህ እና እነ ወ/ሮ...

የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች ከሳሽ አመልካች ደግሞ ጣልቃ ገብ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪዎች በቀን 11/09/2013 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ የእናታቸው ወ/ሮ ሸዋነሽ ስመኝ... Read more

ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ...

የአሁን አመልካች በምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ/መ/ቁ 47863 እና በመ/ቁ በመ/ቁ 47862 በሁለቱም መዝገቦች ላይ 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው የክስ ይዘትም አመልካች የኢትዮጵያ የፌዴራል ቡና... Read more
1345678910Last
«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

የፍርድ ቤቱ ዳኞች እና የአስተዳደር ዘርፍ የሥራ ክፍሎች...

1421

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ዳኞች እና የአስተዳደር ዘርፍ የሥራ ክፍሎች በ2014 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና በ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከነሐሴ 4-7 ቀን 2014 ዓ.ም ግምገማ አካሄዱ፡፡

የፍርድ ቤቱ ዳኞች ነሐሴ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ያካሔዱት የአንድ ቀን የሥራ አፈጻጸም እና የዕቅድ ግምገማ የተመራው በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት በክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ሲሆን በመድረኩ ላይ የችሎቶች ዕቅድ አዘገጃጀትን የተመለከተ ማብራሪያም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ፍርድ ቤቱ ሐሰተኛ የቃለ-መሐላ አቤቱታ ያቀረቡ ባለጉዳይን...

1385

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሶስተኛ ሰበር ችሎት ሐሰተኛ ቃለ-መሐላ አቤቱታ ያቀረቡ ባለጉዳይን በችሎት መድፈር ጥፋተኛ ናቸው በማለት ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት በአንድ ወር ከአስራ አምስት ቀን ቀላል እስራት እንዲቀጡ ወሰነ፡

ፍርድ ቤቱ በእስራት እንዲቀጡ የወሰነባቸው አቶ ኃይለማርያም ወዳጆ በደሀ ደንብ መስቀልኛ የሰበር አቤቱታ ለማቅረብ የዳኝነት ለመክፈል ምንም ሀብት እና ንብረት የሌላቸውና በቀበሌ ቤት የሚኖሩ መሆኑን በቃለ-መሐላ በማረጋገጥ አቤቱታቸውን በሀሰተኛ መንገድ በማቅረባቸው ነው፡፡

ዜና መግለጫ

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከነሐሴ 1-30 ባለው ጊዜ መደበኛ የዳኝነት አገልግሎት መስጠታቸውን ይቀጥላሉ

4636

በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 38(2) መሰረት የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 ባለው ጊዜ ዝግ እንደሚሆኑ ይደነግጋል፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ዳኞች ባላቸው የትርፍ ጊዜ አስቸኳይ የሆኑ ጉዳዮችን ብቻ ሊያስተናግዱ እንደሚገባም አዋጁ ያስቀምጣል፡፡ ዳኞች ዓመቱን ሙሉ እጅግ አድካሚ የሆነ የዳኝነት አግልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ በዚህም አዎንታዊ የሆኑ ውጤቶች ተገኝተዋል፡፡ ይህን ስራ ይበልጥ ለማስቀጠል፣ ወደ 2015 ዓ.ም የሚያልፉ መዝገቦችን ቁጥር ለመቀነስ፣ የበሰሉ መዝገቦችን እልባት ለመስጠት፣ እስረኛ ያለባቸውን መዝገቦች ቅድሚያ ሰጥቶ ለመስራት እንዲያስችል በዳኞች ፈቃደኝነት ላይ በመመስረት የፌዴራል ፍርድ ቤቶቹ ከነሐሴ 1-30/2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ መደበኛውን የዳኝነት አገልግሎት መስጠታቸውን የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡

«ትልቁ የመሪዎች መለያ አውቃለሁ ባይነት ሳይሆን ለመማር...

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ

1494

ክብርት ፕሬዚደንትዋ ይህን የገለጹት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንትና የፌደራል ፍርድ ቤቶች ቃል አቀባይ የሆኑት ክቡር አቶ ተስፋዬ ንዋይ «የአመራር ክህሎት» በሚል ርዕስ ያሳተሙትን መጽሐፍ ሐምሌ 2 ቀን 2014 ዓ.ም በሐያት ሪጀንሲ ሆቴል ለማስመረቅና ለማስገምገም በተዘጋጀ ሥነሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡

First5051525355575859Last