የፌደራል ዳኞች የሥነምግባር እና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ዓለም አቀፋዊ የዳኝነት መርሆዎችን እንዲሁም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግሥትን እና ሌሎች የአገሪቱን ሕጎች መሠረት በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑን ረቂቅ ደንቡ ሲዘጋጅ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው ዓለም አቀፍ የሕግ አማካሪ የሆኑት አሜሪካዊው ሚስተር ማይክል ከኒፍ ገለጹ፡፡
የፌደራል ፍርድ ቤቶች ሪፎርም አካል በሆነውና ማሻሻያ ተደርጎበት በቅርቡ በዳኝነት አስተዳደር ጉባኤ በጸደቀው የፌደራል ዳኞች የሥነምግባር እና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ላይ ለፌደራል ፍርድ ቤት ዳኞች በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል ከነሐሴ 15-25 ቀን 2013 ዓ.ም በአምስት ዙሮች በመሰጠት ላይ ነው፡፡