የሰበር ውሳኔዎች

 

ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት...

በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ  የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ ትርጉም... Read more

ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት...

ከ2002 ዓ.ም እስከ 2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔዎችን ያጠቃለለ መጽሐፍ በልዮ ዕትም ለንባብ ምቹ ሆኖ ቀርቧል። Read more

ወ/ሮ የማርውሃ ወርቅነህ እና እነ ወ/ሮ...

የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች ከሳሽ አመልካች ደግሞ ጣልቃ ገብ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪዎች በቀን 11/09/2013 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ የእናታቸው ወ/ሮ ሸዋነሽ ስመኝ... Read more

ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ...

የአሁን አመልካች በምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ/መ/ቁ 47863 እና በመ/ቁ በመ/ቁ 47862 በሁለቱም መዝገቦች ላይ 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው የክስ ይዘትም አመልካች የኢትዮጵያ የፌዴራል ቡና... Read more
1345678910Last
«November 2025»
MonTueWedThuFriSatSun
272829303112
3456789
10111213141516
17181920212223
24252627282930
1234567

ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ...

1375

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሹመታቸውን ያጸደቀላቸው የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን አመራሮች የቃለመሀላ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ የካቲት 14 ቀን 2014 ዓ.ም አስፈጽመዋል፡፡

ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ስራ ውጤታማ የሚሆነው ከባለድርሻ አካላት እና ከሕብረተሰቡ አስፈላጊው ትብብርና ድጋፍ ሲሰጠው መሆኑን በቲውተር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

ክብርት ፕሬዝደንቷ ከምክክር ኮሚሽኑ ብዙ ይጠበቃልም ብለዋል::

የፍርድ ቤቱ አስተዳደር ዘርፍ አፈጻጸም ከፍተኛ መሻሻል...

1347

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ዘርፍ የስራ ክፍሎች አፈጻጸም ከፍተኛ መሻሻል ያሳየ መሆኑን የ2014 መጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምገማ ውጤት ማመልከቱ ተገለጸ፡፡ 

በዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረኩ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ የተገኙ ሲሆን የቀረበውን የማጠቃለያ ሪፖርት መሰረት በማድረግ በሰጡት አስተያየት በአስተዳደር ዘርፉ እየተመዘገበ ያለው አመርቂ አፈጻጸም በፍርድ ቤቶች እየተከናወኑ ያሉ የማሻሻያ ስራዎች ፍሬ እያፈሩ ስለመምጣታቸው ያላቸውን እርግጠኝነት ከፍ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ለአራት ክልሎች ጠቅላይ ፍ/ቤቶች የቁሳቁስ...

1344

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አራት የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2014 ዓ.ም የሰባት ሚሊዮን ብር ግምት ያለው የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡

የቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው ለአማራ እና ለአፋር ክልሎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች እንዲሁም በቅርቡ በአዲስ መልክ በክልልነት የተቋቋሙትን የሲዳማ እና የደቡብ ምዕራብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር ነው፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት...

1237

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የተወሰዱ እርምጃዎች

የካቲት 6 ቀን 2014 ዓ.ም «የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ» ዓመታዊ ጉባኤ ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ባቀረቡት ሪፖርት በ2013-2014 በጀት ዓመት አጋማሽ በፍርድ ቤቱ የሪፎርም ሥራዎች ዙሪያ የተከናወኑ ተግባራትን ዳስሰዋል፡፡ ክብርት ፕሬዚደንትዋ ዛሬም ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል ባይባልም የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የተለያዩ እርምጃዎች የተወሰዱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ይህ የገለልተኝነት እና የነጻነት ጉዳይ ዳኞች ከውጭም ሆነ ከውስጥ ጣልቃ ገብነት ተጽዕኖ ሳይደርስባቸው ሕግን ብቻ ተከትለው ውሳኔ እንዲሰጡ አስፈላጊ ሁኔታዎችን ማመቻቸትን ይጠይቅ ነበር ብለዋል፡፡ የዳኝነት ነጻነት የዳኞች ነጻነት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ፍ/ቤቱም እንደተቋም ለማንኛውም የፖለቲካም ሆነ ማህበራዊ ጫናዎች የተጋለጠ እንዳይሆን አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እና እርምጃዎችንም መውሰድ ይጠይቅ እንደነበር ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡ እንደተከናወኑ ከጠቀሷቸው ተግባራት መካከል፡-

First5455565759616263Last