የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በፌደራል ፍርድ ቤቶች የኢፋይሊንግ፣ ኢሊቲጌሽን እና ኤሌክትሮኒክ ሪከርድ አመራር የአፈጻጸም ረቂቅ መመሪያ ላይ ከፌደራል ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ ሃላፊዎችና ተጠሪ ዳኞች፣ ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ከፌደራል ማረሚያ ቤት፣ ከኢትዮ ቴሌኮም፣ ከኢንፎርሜሽንና መረብ ደህንነት አስተዳደር፣ ከፌደራል ፖሊስ፣ ከፍትህ ሚኒስቴር፣ ከፌደራል ጠበቆች ማህበር፣ ከህግ ባለሙያዎች ማህበር እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በቀን 19/04/2017 ዓ.ም የውይይት መድረክ ተካሂዷል።