የሰበር ውሳኔዎች

 

ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት...

በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ አስተዳደራዊ ተግባርን ለማከናወን በተሰማሩ ሰራተኞች የሚነሱ  የስራ ክርክሮችን በተመለከተ ፍርድ ቤቶች የስራ ክርክሩን ተቀብለው አከራክረው ለመወሰን ህጋዊ የዳኝነት ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ ትርጉም... Read more

ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት...

ከ2002 ዓ.ም እስከ 2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔዎችን ያጠቃለለ መጽሐፍ በልዮ ዕትም ለንባብ ምቹ ሆኖ ቀርቧል። Read more

ወ/ሮ የማርውሃ ወርቅነህ እና እነ ወ/ሮ...

የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች ከሳሽ አመልካች ደግሞ ጣልቃ ገብ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪዎች በቀን 11/09/2013 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ የእናታቸው ወ/ሮ ሸዋነሽ ስመኝ... Read more

ጨመሬ ቶሎሳ እና የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ...

የአሁን አመልካች በምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ/መ/ቁ 47863 እና በመ/ቁ በመ/ቁ 47862 በሁለቱም መዝገቦች ላይ 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ በአመልካች ላይ ያቀረበው የክስ ይዘትም አመልካች የኢትዮጵያ የፌዴራል ቡና... Read more
12345678910Last
«March 2026»
MonTueWedThuFriSatSun
2324252627281
2345678
9101112131415
16171819202122
23242526272829
303112345

የሌሎችን  የሥነምግባር ችግር ከሚዳኘው የዳኝነት ተቋም...

2029

ሕብረተሰቡ ከዳኞች የሚጠብቀውን የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት መጀመሪያ ዳኞች በላቀ የሥነምግባር ደረጃ ላይ ሊገኙ እንደሚገባ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ብርሐነመስቀል ዋጋሪ ገለጹ፡፡

ከፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች በፌዴራል ዳኞች ሥነምግባርና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ላይ ለሁለተኛ ዙር በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከመስከረም 14-15 ቀን 2014 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው ቲኬ ኢንተርናሽናል ሆቴል ተሰጥቷል፡፡

ክቡር ፕሬዚደንቱ በግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በፍርድ ቤቶች ከትናንት ይልቅ ዛሬ የዳኝነት ነጻነትና ተጠያቂነት አተገባበር እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቁመው ይህንም በፍ/ቤቶች ረዘም ያለ ቆይታ ያላቸው ዳኞች የሚገነዘቡት ነው ብለዋል፡፡

የፍርድ ቤቱ ሠራተኞች ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀንን አከበሩ

2037

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ23ኛ ጊዜ በመከበር ላይ የሚገኘው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ “በትዉልድ ቅብብሎሽ ኢትዮጵያ ትፀናለች” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኝ ሲሆን ቀኑ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሠራተኞች ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ/ም በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ፡፡

በዓሉ በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ሲከበር የፍርድ ቤቱ ሴቶችና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ወርቅነሽ በቀለ ባደረጉት የመክፈቻ ላይ ንግግር እንደገለጹት ከሰባት ቢሊዮን በላይ ከሚገመተዉ የዓለም ህዝብ መካከል የወጣቱ ቁጥር 1.8 ቢሊዮን እንደሚደርስና ከዚህ ውስጥ 90 ከመቶ የሚሆነዉ ወጣት በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት እንደሚገኝ ጠቅሰው ከሀገራችን የህዝብ ብዛትም 31.8 በመቶ ያህሉ ከፍተኛ አቅም ያለዉ አምራች ኃይል የሆነዉ የወጣቱ ክፍል መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ዳኞች በማያቋርጥ ሒደት ብቃታቸውን ሊያሳድጉና በሥልጠና...

2048

ዳኞች በማያቋርጥ ሒደት ብቃታቸውን ሊያሳድጉና በሥልጠና ሊያልፉ እንደሚገባ ተጠቆመ።

ዳኞች በማያቋርጥ ሒደት ብቃታቸውን ሊያሳድጉና በሥልጠና ሊያልፉ እንደሚገባ ይህም የዳኝነት ነጻነትን ለማስጠበቅና ክህሎታቸውን ለማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ም/ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ተþሊት ይመስል ገለጹ፡፡

ከፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ ከፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት እና ከፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የተውጣጡ 350 ያህል የፌደራል ፍ/ቤቶች ዳኞች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከነሐሴ 21-22 ቀን 2014 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ተካሒዷል፡፡

የፍርድ ቤቱ ዳኞች እና የአስተዳደር ዘርፍ የሥራ ክፍሎች...

1926

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ዳኞች እና የአስተዳደር ዘርፍ የሥራ ክፍሎች በ2014 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና በ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከነሐሴ 4-7 ቀን 2014 ዓ.ም ግምገማ አካሄዱ፡፡

የፍርድ ቤቱ ዳኞች ነሐሴ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ያካሔዱት የአንድ ቀን የሥራ አፈጻጸም እና የዕቅድ ግምገማ የተመራው በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት በክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ሲሆን በመድረኩ ላይ የችሎቶች ዕቅድ አዘገጃጀትን የተመለከተ ማብራሪያም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

First6061626365676869Last