የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች የሥልጠና ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት፣የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሥልጠና መመሪያ፣የእግድ አሰጣት እና አተገባበር ላይ፣በፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍትሕ መዘግየት ምክንያቶች እና ማነቆዎች በሚል በተዘጋጀ ሞጁል ላይ እንዲሁም የወሲባዊ ጥቃት ወንጀሎችን በተፋጠነ እና ተጎጅ ተኮር በሆነ መንገድ ለመዳኘት የሚያግዝ ማኑዋል ላይ ለሁለት ቀናት የቆየ የውይይትና ግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል፡፡