የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያዘጋጀውን እና በፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ውይይት ተደርጎበትና ቅቡልነት አግኝቶ ለትግበራ ዝግጁ የሆነውን “በዳኝነት አካል ውስጥ የሚታዩ የሙስና ተግባራት መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ስትራቴጂ” የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ የምድብ ችሎት ተጠሪ ዳኞች፣ ሰብሳቢ ዳኞች፣ የዳኞች ተወካዮች እና የአስተዳደር ዘርፍ ልዩ ልዩ የስራ ክፍል ሃላፊዎች በተሳተፉበት የውይይት መድረክ ይፋ አድርጓል፡፡
ስትራቴጂው ይፋ የተደረገበት የውይይት መድረክ ለስትራቴጂው አተገባበር የሚገጁ ሃሳቦችን በማንሸራሸር ይሁንታ ለመስጠት የተዘጋጀ ነው፡፡