በመቀሌ ስካሄድ የነበረዉ የፌደራል እና የክልል ፍርድ ቤቶች ምክክር መድረክ በስኬት ተጠናቀቀ

36
(ግንቦት 19/2015 ዓ.ም) በአዉሮፓ ህብረት ቴክኒካዊ ድጋፍ በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሪፎርም የሚደግፍ ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተከናወነ የመሚገኘኝ ሲሆን ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ መንግስት የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሪፎርም ሥራዎች የሚደግፍና የፌደራል ፍርድ ቤቶች እና የክልል ፍርድ ቤቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነዉ።

በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት ተካሔደ • ከፍ/ቤቱ በጡረታ ለተሰናበቱ የቀድሞ ሠራተኞች የምስጋና መርሐ-ግብር ተከናውኗል

48
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ዘርፍ የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የተዘጋጀ ውይይት በፍ/ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

የሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በሕጻናት የቅብብሎሽ ሥርዓት ላይ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ተካሔደ

49
በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በፍትሕ ሥርዓቱ ውስጥ የሚያልፉ ሕጻናት የዘርፈ-ብዙ አገልግሎት ተጠቃሚ በሚሆኑበት የቅብብሎሽ ሥርዓት ዙሪያ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ጎልድ ማርክ ሆቴል ተካሂዷል፡፡

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የምርምር እና ሕግ ጉዳዮች ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አሮን ደጎል በቅርቡ በፍ/ቤቱ ጸድቆ ከሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ስለሆነው የሰበር ችሎት ሥነሥርዓት መመሪያ ቁጥር 17/2015 አስመልክቶ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ወቅታዊና ልዩ ልዩ በሚል ዓምድ ላይ ሰኞ ሚያዝያ 30 ቀን

149
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የምርምር እና ሕግ ጉዳዮች ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አሮን ደጎል በቅርቡ በፍ/ቤቱ ጸድቆ ከሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ስለሆነው የሰበር ችሎት ሥነሥርዓት መመሪያ ቁጥር 17/2015 አስመልክቶ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ወቅታዊና ልዩ ልዩ በሚል ዓምድ ላይ ሰኞ ሚያዝያ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ቀርበው የሰጡት ማብራሪያ ገፅ 10 እና 11 ላይ ይመልከቱ ፡፡

በፍርድ ቤቱ የተጀመረውን የማሻሻያ ሥራ ሊሸከም የሚችልና የሥነምግባር መርሆዎችን በአግባቡ የተገነዘበ ባለሙያ ማፍራት እንደሚገባ ተገለጸ

61
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳኝነት አገልግሎት ዘርፍ እና በአስተዳደር ሥራዎች ዘርፍ የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎችን ሊሸከም የሚችልና የሥነምግባር መርሆዎችን በአግባቡ የተገነዘበ፣ በሥነምግባር እሴቶች እየተመራ ኃላፊነቱን እና ሥራውን በአግባቡ ሊያከናውን የሚችል የፍርድ ቤት ማሕበረሰብ መገንባት አስፈላጊ መሆኑን በፍርድ ቤቱ የክቡር ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጃ ታደሰ ገለጹ፡፡
ለፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎችና ቡድን መሪዎች በሥነምግባር፣ በሙስና እንዲሁም ተያያዥ በሆኑ ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ የተዘጋጀ የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ተሰጥቷል፡፡

“ሙስናና ብልሹ አሠራርን መከላከልና መልካም ሥነምግባርን ማስፈን” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሥልጠና ለፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ዘርፍ ሠራተኞች ተሰጠ

43
ለፍርድ ቤቱ አዲስ ሠራተኞች የሙያ ትውውቅ ኮርስ (Induction Training) ተሰጠ
--------------------------------------------------------------------------
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሥነምግባር መከታተያ ክፍል “ሙስናና ብልሹ አሠራርን መከላከልና መልካም ሥነምግባርን ማስፈን” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሥልጠና ከፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ዘርፍ ለተውጣጡ 120 ሠራተኞች ሚያዚያ 21 ቀን 2015 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ተሰጠ፡፡

የአውሮፓ ሕብረት ለፍርድ ቤቱ በሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ለሚከናወኑ ሥራዎች አፈጻጸም ተገቢው ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ተመለከተ

89
በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት በፌደራል ፍርድ ቤቶች ተግባራዊ እንዲሆኑ ለተለዩ የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ሥራዎች ማስፈጸሚያ የአውሮፓ ሕብረት የመደበው የገንዘብ ድጋፍ ውጤታማ በሆነ መንገድ ጥቅም ላይ እንዲውል የፍርድ ቤቱ አመራሮችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተገቢውን ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡

አጣሪ ጉባዔው በአራት ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

115
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሐሙስ መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በአራት ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ሶስት ጉዳዮች ላይ ለውሳኔ አሰጣጥ እንዲያመች ተጠሪዎች መልስ እንዲሰጡበት አቅጣጫ ሲያስቀምጥ በአንድ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ መረጃዎች ተጣርተው እንዲቀርቡ ትእዛዝ በማስተላለፍ በይደር አሳልፎታል፡፡
1345678910Last