በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ሲመክር የቆየው ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች መድረክ የጋራ አቋም በመያዝ ተጠናቋል፡፡
/ Categories: News

በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ሲመክር የቆየው ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች መድረክ የጋራ አቋም በመያዝ ተጠናቋል፡፡

ለሁሉም ፍርድ ቤቶች የጋራ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ በመወያየት የዳኞች ያለመከሰስ መብት በህገ- መንግስቱ ላይ በተቀመጠ መሰረት ተግባራዊ ባልተደረገባቸው ክልሎች የህግ ማዕቀፍ እንዲኖር፣ሁሉም ፍርድ ቤቶች የአገልግሎት አሰጣጣቸዉን እንዲያዘምኑ የሚያደርግ የቴክኖሎጂ መሰረት ልማትን የሚዘረጉበት በቂ በጀት እንዲያገኙ ሁሉም ትብብር እንዲያደርግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየተወያዩ መፍትሔ ለማምጣት የጋራ አቋም ተይዟል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር በሀገር አቀፍ ደረጃ የፍርድ ቤቶችን አሰራር በቴክኖሎጂ የታገዘ እና ቀልጣፋ ለማድረግ በተቀናጀ መልኩ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በማድረግ የዳኝነት አገልግሎት ጥራት፣ ተደራሽነትንና ፍትሃዊነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉብኝትና የምርቃት ፕሮግራም የሚካሄድ ይሆናል፡፡

Previous Article ኒታ (National Institute for Trial Advocacy (NITA)) እና ጆንስ ዴይ (JONES DAY) የተባሉ መቀመጫቸውን አሜሪካን ሀገር ያደረጉ ግብረሰናይ ድርጅቶች ከፍተኛ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ልዑካን ቡድን በጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመገ
Next Article የሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህንጻ እድሳትና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች ምርቃት እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጉብኝት ተካሄደ
Print
669