ሀገር አቀፍ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የጋራ መድረክ ተጠናቀቀ

539

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አመታዊ ሀገር አቀፍ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ (ጆይንድ አፕ ጀስቲስ ፎረም) የፌዴራልና የክልል የዳኝነትና የፍትህ አካላት የጋራ መድረክ የመግባቢያ ሰነድ የፊርማ ስነ ስርዓት በማከናወን ተጠናቋል።

የዳኝነትና የፍትህ አካላት በጋራ የሚመክሩበት፣ የሚወያዩበትና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጡበት ሀገር አቀፍ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

433

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በመክፈቻ ንግግራቸው፤ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠባት እና ፍትሕ የሰፈነባት ሀገር ከመገንባት አንጻር በጋራ ስራዎች ላይ ለመምከርና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ የመድረኩ ሚና ከፍተኛ እንደሆነ በማንሳት፤ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በጋራ በመፍታት ተቋማዊም ሆነ የወል ግቦችን ማሳካት እንደሚቻል ገልጸዋል።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል ህግ ትርጉም ውሳኔዎች ስብስብ ልዩ ዕትም እና የስልጠና ማኑዋሎችን የማስተዋወቅ ፕሮግራም ተካሄደ

594

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአውሮፓ ህብረት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ሁለት የስልጠና ማኑዋሎች ማለትም ተከታታይ የወንጀል ችሎት አመራር ሥልጠና ማንዋል( Training Manual on continuous criminal trials )፣ ድንበር ተሻጋሪ እና ከባድ ወንጀሎች ሥልጠና ሞጁል(Training Module on Trans-Boundary and grave crimes) እንዲሁም "በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል ህግ ትርጉም ውሳኔዎች ስብስብ በጉዳዮች የተደራጁ ልዩ ዕትም" መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማስተዋወቅ ፕሮግራም አካሂዷል ፡፡

በፍትህ ስርአቱ ውስጥ ለሚያገለግሉ የሶሻል ወርክ ባለሞያዎች የሚውል የስልጠና ማኑዋል የመጀመሪያ ረቂቅ ላይ ውይይት ተደረገ

592

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የተባባሩት መንግስታት የህዝብ ፈንድ(UNFPA) የጋራ ትብብር በፍትህ ስርአት ውስጥ የሚገለግሉ የሶሻል ወርክ ባለሞያዎችን እውቀት እና ከህሎት በተሻለ ለመገንባት እየተዘጋጀ የሚገኘው የስልጠና ማኑዋል ረቂቅ ላይ የውይይት እና ግብአት ማሰባሰቢያ መድረክ በቀን 12/7/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አለም አቀፉን የሴቶች ቀን አከበሩ

609

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዘንድሮ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ማርች 8 በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ GIVE TO GAIN በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ "የሴቶች ድምጽ ለዕኩልነት እና ለበለጸገች ኢትዮጵያ "በሚል መሪ ቃል መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ተከብሯል፡፡

124678910Last