የፍርድ ቤቱ አስተዳደር ዘርፍ አፈጻጸም ከፍተኛ መሻሻል ያሳየ መሆኑ ተገለጸ

372

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ዘርፍ የስራ ክፍሎች አፈጻጸም ከፍተኛ መሻሻል ያሳየ መሆኑን የ2014 መጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምገማ ውጤት ማመልከቱ ተገለጸ፡፡ 

በዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረኩ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ የተገኙ ሲሆን የቀረበውን የማጠቃለያ ሪፖርት መሰረት በማድረግ በሰጡት አስተያየት በአስተዳደር ዘርፉ እየተመዘገበ ያለው አመርቂ አፈጻጸም በፍርድ ቤቶች እየተከናወኑ ያሉ የማሻሻያ ስራዎች ፍሬ እያፈሩ ስለመምጣታቸው ያላቸውን እርግጠኝነት ከፍ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ለአራት ክልሎች ጠቅላይ ፍ/ቤቶች የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

319

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አራት የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2014 ዓ.ም የሰባት ሚሊዮን ብር ግምት ያለው የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡

የቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው ለአማራ እና ለአፋር ክልሎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች እንዲሁም በቅርቡ በአዲስ መልክ በክልልነት የተቋቋሙትን የሲዳማ እና የደቡብ ምዕራብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር ነው፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የተወሰዱ እርምጃዎች

310

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የተወሰዱ እርምጃዎች

የካቲት 6 ቀን 2014 ዓ.ም «የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ» ዓመታዊ ጉባኤ ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ባቀረቡት ሪፖርት በ2013-2014 በጀት ዓመት አጋማሽ በፍርድ ቤቱ የሪፎርም ሥራዎች ዙሪያ የተከናወኑ ተግባራትን ዳስሰዋል፡፡ ክብርት ፕሬዚደንትዋ ዛሬም ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል ባይባልም የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነት እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የተለያዩ እርምጃዎች የተወሰዱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ይህ የገለልተኝነት እና የነጻነት ጉዳይ ዳኞች ከውጭም ሆነ ከውስጥ ጣልቃ ገብነት ተጽዕኖ ሳይደርስባቸው ሕግን ብቻ ተከትለው ውሳኔ እንዲሰጡ አስፈላጊ ሁኔታዎችን ማመቻቸትን ይጠይቅ ነበር ብለዋል፡፡ የዳኝነት ነጻነት የዳኞች ነጻነት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ፍ/ቤቱም እንደተቋም ለማንኛውም የፖለቲካም ሆነ ማህበራዊ ጫናዎች የተጋለጠ እንዳይሆን አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እና እርምጃዎችንም መውሰድ ይጠይቅ እንደነበር ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡ እንደተከናወኑ ከጠቀሷቸው ተግባራት መካከል፡-

«የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ እና የወደፊት ዕይታ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መድረክ ተካሔደ

600

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ «የፌደራል ፍርድ ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ እና የወደፊት ዕይታ /State of the Judiciary/» በሚል ርዕስ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀ ጉባዔ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ የካቲት 6 ቀን 2014 ዓ.ም ተካሔደ፡፡

የመጀመሪያው ጉባዔ በ2012 የተካሔደ ሲሆን መድረኩ በኮቪድ 19 ምክንያት ተቋርጦ ከቆየ በኋላ ሁለተኛው ጉባዔ በፌደራል ፍርድ ቤቶች በ2013 በጀት ዓመት እና በ2014 ግማሽ በጀት ዓመት በተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ተከናውኗል፡፡

የቅድመ መዋቅር ነባራዊ ሁኔታ ትንተና  እና ረቂቅ ተቋማዊ ለዕላዊ መዋቅር ላይ ውይይት ተካሄደ

410

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተቋማዊ መዋቅርን እንዲሰራ በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት - በፍትህ ፕሮጀክት የተቀጠረ እማካሪ ድርጅት ያካሄደውን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ነባራዊ ሁኔት ትንተና ውጤት በፍርድ ቤቱ በኩል ስራውን እንዲከታተል ለተቋቋመ አብይ ኮሚቴ አቀረበ።

አማካሪ ድርጅቱ ( HST) ቀደም ሲል እያካሄደ ያለውን ጥናት በተደጋጋሚ ለዐብይ ኮሚቴው በማቅረብና የጥናት ስልት፣ ሂደት፣ ይዘት እና ወስን ላይ የማዳበሪያ እና አቅጣጫ ጠቋሚ ሃሳቦችን ሰብስቧል።

የዳኝነት ስርዓቱን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ፍርድ ቤቱ ከማህበሩ ጋር አብሮ እንደሚሰራ ተገለጸ

275

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት ስርዓቱን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት በቅርቡ ከተቋቋመው የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ገለጹ፡፡

ክቡር አቶ ሰለሞን ይህን የገለጹት በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው በአዲሱ የፌደራል የጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ መሰረት ለተቋቋመው የጠበቆች ማህበር ስራ ማስጀመሪያ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በእንግድነት ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው፡፡

ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ በሰጡት የማጠቃለያ አስተያየት ካነሷቸው ነጥቦች መካከል ዋና ዋናዎቹ

293

ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ (የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚደንት) ጥር 9 ቀን 2014 ዓ.ም «ፍርድ ቤቶች እና የሽግግር ፍትሕ፤ ግጭቶች ሲከሰቱ ወይም ከግት በኋላ» በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ሲምፖዚየም ላይ ከተሳታፊዎች የቀረቡ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ በሰጡት የማጠቃለያ አስተያየት ካነሷቸው ነጥቦች መካከል ዋና ዋናዎቹ፡-

• ሲምፖዚየሙን ማዘጋጀት ያስፈለገው አሁን አገራችን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ የዳኝነት ተቋሙ ሊኖረው ከሚችለው የዳኝነት ሚና ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡

በፌዴራል ፍ/ቤት ተዘዋዋሪ ችሎት 204 ፋይሎች ታይተው 68 ፋይሎች እልባት ማግኘታቸው ተገለጸ

304

በፌዴራል ፍ/ቤት ተዘዋዋሪ ችሎት 204 ፋይሎች ታይተው 68 ፋይሎች እልባት ማግኘታቸው ተገለጸ

በተለያየ የሃራችን ክፍሎች የተፈጠሩ ግጭቶች ጋር በተገናኘ በፌዴራል ፍ/ቤት ተዘዋዋሪ ችሎት 204 ፋይሎች ታይተው 68 ፋይሎች እልባት አግኝተዋል፡፡

በእያንዳንዱ ፋይል የተከሳሾች ቁጥር በአማካይ ከ 50 – 200 እንደሚድረስ የገለጹት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ ጉዳዩቹ ደግሞ እጅግ ውስብስብ ናቸው ብለዋል፡፡

ክብርት ፕሬዚደንትዋ «ፍርድ ቤቶች እና የሽግግር ፍትሕ፤ ግጭቶች ሲከሰቱ ወይም ከግጭት በኋላ » በሚል ርዕስ በስካይ ላይት ሆቴል ጥር 9 ቀን 2014 ዓ.ም በተዘጋጀ ሲምፖዚየም መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር በሀገራችን በተከሰቱ ግጭቶች ሕግንና ሞራልን የጣሱ በርካታ ተግባሮች እንደተከናወኑ ገልጸው በሴቶች እና ሕጻናት ላይ የተፈጸመው ወንጀል ደግሞ ሊታለፉ ከማይገባቸው ወንጀሎች የሚመደብ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

First567810121314Last