የላይቤሪያ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንትና ልዑክ ቡድናቸው በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጉብኝት አደረጉ

253

የላይቤሪያ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ጄሚ ኩዊኪ (Honorable Jamie Quiqui Gbeisay) እና ልዑክ ቡድናቸው በቀን 17/03/2018 ዓ.ም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉብኝት አድርገዋል፡፡

በዲጂታል የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ በዋነኝነትም በኢንቲግሬትድ ኬዝ ማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም (ICMIS) ሲስተም ላይ ከቀን 06-07/03/2018 ዓ.ም ለሁለት ቀናት ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ሲሰጥ የቆየው የተግባር ልምምድ (ስልጠና) ተጠናቀቀ ።

337

በስልጠናው የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ድሪባ ፈዬራ ክቡራን ዳኞች ላደረጉት ንቁ ተሳትፎና በመድረኩ ለተነሱት ገንቢ ሀሳብ አስተያየቶች አመስግነው ቴክኖሎጂው በቅርቡ ወደ ትግበራ ስለሚገባ ለትግበራው ውጤታማነት ስልጠናው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በአገልግሎት አሰጣጥና የደንበኞች አያያዝ ላይ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ

440

የፌደራል የህግና የፍትሕ ኢንስቲትዩት ለተከታታይ ሦስት ሳምንታት በሶስት ዙር ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች፣ከፍትሕ ሚኒስቴር እንዲሁም ከፌዴራል የሕግና የፍትሕ ኢንስቲትዩት ለተውጣጡ 170 የአስተዳደር ሰራተኞች ከጥቅምት 21 ቀን እስከ ህዳር 6ቀን 2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል፡፡

የተግባር ልምምድ (ስልጠና) በዲጂታል የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች እየተሰጠ ይገኛል

406

በዲጂታል የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከቀን 06-07/03/2018 ዓ.ም ለሁለት ቀናት የሚቆይ የተግባር ልምምድ (ስልጠና) ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች እየተሰጠ ይገኛል።

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሪሶርስ ኢንሪቺንግ አፍሪካን ላይቭስ በሚባል ግብረ ሰናይ ድርጅት አስተባባሪነት የተሰበሰቡ መጽሃፍቶችን ተረከበ

293

ሪሶርስ ኢንሪቺንግ አፍሪካን ላይቭስ በመባል የሚጠራ ግብረ ሰናይ ድርጅት ቡክስ ፎር አፍሪካና ቶምሰን ሪዉተርስ ከሚባሉ ለጋሽ ድርጅቶች ለትምህርት ቤቶች እና ለፍትህ ተቋማት የሚያገለግሉ መጻሃፍቶችን በማሰባሰብ ወደ አገር ውስጥ እንዲገባ አድርጓል፡፡

በአስማሚነት ክህሎት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረዉ የተግባር ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

455

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት ከጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ 4 ቀናት በተግባር ሲሰጥ የነበረዉ የአስማሚነት ክህሎት ስልጠና ተጠናቋል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የሶማሊ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቴክኖሎጂ ስራዎችን በይፋ አስጀመሩ

733

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የሶማሊ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቪድዮ ኮንፍረንስ፣በሶማሊኛ ቋንቋ የሚሰራ የመዝገብ አስተዳደር፣ የኢፋይሊንግ አገልግሎት እንዲሁም የቀጠሮ መከታተያ አገልግሎትን በቀን 12/02/2018 ዓ.ም የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ክቡራን ፕሬዝደንቶች ባሉበት በይፋ አስጀምረዋል፡፡

የሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህንጻ እድሳትና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች ምርቃት እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጉብኝት ተካሄደ

623

የሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የድሬዳዋ አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የህንጻ እድሳትና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች ምርቃት በቀን 11/02/2018 ዓ.ም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት፣ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ የሀረሪ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ ሱልጣን አ/ሰላም እንዲሁም የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ክቡራን ፕሬዝደንቶች ባሉበት ተካሂዷል፡፡

245678910Last