በፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ ላይ ለዳኝነት ዘርፉ ድጋፍ ሰጪ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ

1977

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከዳኝነት ዘርፉ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ላላቸው ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች በፍትሐብሔርጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ ላይ በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል ነሐሴ 15 ቀን 2013 ዓ.ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

በሥልጠናው የተሳተፉት ብዛታቸው 65 የሆኑ የፍርድ ቤቱ ረዳት ዳኞች፣ ሴክሬታሪዎች፣ የችሎት ፀሐፊዎች፣ ሬጅስትራሮች እና ዳታ ኢንኮደሮች ናቸው፡፡

የፌደራል ዳኞች የሥነምግባር እና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ዓለም አቀፋዊ የዳኝነት መርሆዎችን መሠረት በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ

2327

የፌደራል ዳኞች የሥነምግባር እና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ዓለም አቀፋዊ የዳኝነት መርሆዎችን እንዲሁም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግሥትን እና ሌሎች የአገሪቱን ሕጎች መሠረት በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑን ረቂቅ ደንቡ ሲዘጋጅ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው ዓለም አቀፍ የሕግ አማካሪ የሆኑት አሜሪካዊው ሚስተር ማይክል ከኒፍ ገለጹ፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ሪፎርም አካል በሆነውና ማሻሻያ ተደርጎበት በቅርቡ በዳኝነት አስተዳደር ጉባኤ በጸደቀው የፌደራል ዳኞች የሥነምግባር እና የዲሲፒሊን ክስ ሥነሥርዓት ደንብ ላይ ለፌደራል ፍርድ ቤት ዳኞች በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል ከነሐሴ 15-25 ቀን 2013 ዓ.ም በአምስት ዙሮች በመሰጠት ላይ ነው፡፡

በፍርድ ቤቱ የፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው

1797

በቅርቡ የፀደቀውን የፌደራል ፍርድ ቤቶች የፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ በ2014 ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊው ቅድመ-ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 008/2013ን ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ለማስተዋወቅና ትግበራውን ለማስጀመር ነሐሴ 8 ቀን 2012 ዓ.ም በራዲሰን ብሉ ሆቴል ውይይት ተካሒዷል፡፡

በፍ/ቤቶች የዳኝነት ነጻነትን፣ ገለልተኝነትን እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተገለጸ

1557

በፌደራል ፍርድ ቤቶች ካለፈው ዓመት ጀምሮ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞችን እና ተቋማዊ ነጻነትን፣ ገለልተኝነትን እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የተወሰዱ እርምጃዎች ለማሻሻያ ስራው መሰረት የጣሉ እና ውጤታማ እንደነበሩ ተገለጸ፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ በፌደራል ፍርድ ቤቶች፣ በዳኞች አስተዳደር እና በሕገመንግሥት አጣሪ ጉባዔ የተከናወኑ ተግባራትን እና የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎችን አስመልክቶ ነሐሴ 7 ቀን 2013 ዓ.ም በጽ/ቤታቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ዜና መግለጫ:- ፌዴራል ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ስለመሆናቸው

2007

ፌዴራል ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ስለመሆናቸው

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 ድረስ ዝግ እንደሚሆኑ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 በአንቀጽ 38 ይደነግጋል፡፡ ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቶች የዜጎች መብቶችን የሚያስከብሩ የፍትህ ተቋማት በመሆናቸው እና የፍርድ ቤት ውሳኔና ትዕዛዝ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ወቅታዊ ምላሽ መስጠት ያስችል ዘንድ ፍርድ ቤቶቹ በከፊል ዝግ ሆነው የሚቆዩ ይሆናል፡፡

የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባላት የትውውቅና የቃለ መሐላ መርሐ-ግብር ተካሔደ

1944

የተሻሻለው የፌደራል የዳኝነት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1233/2013 መጽደቁን ተከትሎ አዲስ የተደራጀው የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባላት የትውውቅ እና ቃለ-መሐላ የመፈጸም ሥነሥርዓት ነሐሴ 1 ቀን 2013 ዓ.ም በሒልተን ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ ተካሔደ፡፡

የዳኞች ሥልጠና ፍትሐዊና ተጠያቂነት ያለባቸው ፍርድ ቤቶችን ለመገንባት እንደሚረዳ ተጠቆመ

1725

በፌደራል በጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በዩ.ኤን.ዲፒ (UNDP) መካካል እየተተገበረ ባለው የፍርድ ቤቶች ማሻሻያ ፕሮጀክት አማካኝነት እየተካሄደ በሚገኘው የዳኞች ስልጠና ሥርዓት የዳሰሳ ጥናት ላይ የግብአት ማሰባሰቢያ የውይይት መድረክ ሐምሌ 30 ቀን 2013 ዓ.ም በቤስት ዌስተርን ሆቴል ተካሔደ፡፡

የዳኞችን ዕውቀት እና ክሕሎት በማጎልበት የዳኝነት አገልግሎት አሠጣጥን ጥራት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው

1677

የፌደራል የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓትን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 1183/2012 ላይ ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ከፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለተውጣጡ ዳኞች የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከሐምሌ 24-25 ቀን 2013 ዓ.ም በራዲሰን ብሉ ሆቴል ተሰጠ፡፡

First2829303133353637