በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሕጎችና አዋጆች ሲወጡ ልዩ ትኩረት የሚፈልጉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ

2236

አገራችን በርካታ ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶችን የተቀበለች እና በርካታ የሕግ ድንጋጌዎች ያሏት በመሆኑ ሕጎቹን ትኩረት የሚፈልጉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ማስተካከል፣ ወደፊት የሚወጡ ሕጎችንና አዋጆችን ደግሞ ይህን ታሳቢ ባደረገ ሁኔታ ማየት እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሕግ፣ ዲሞክራሲና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ዕፀገነት መንግሥቱ አስገነዘቡ፡፡

በፌደራል ፍ/ቤቶች የአምስት ዓመት ስትራትጅክ ዕቅድ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ አንድ ግብ የተቀመጠ መሆኑ ተገለጸ

2369

በፌደራል ፍርድ ቤቶች ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ተግባራዊ እየተደረገ በሚገኘው ስትራቴጅክ ዕቅድ ላይ ከተቀመጡ ስድስት ቁልፍ የውጤት መስኮች አንዱ ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት መሆኑንና በዚህ ውስጥ የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደግብ ተይዞ በዚህ ዙሪያ የተለያዩ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደት ክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ገለጹ፡፡

ፍርድ ቤቱ ከጾታዊ ጥቃት ነጻ የሆነ ማህበረሰብ የመገንባት ዓላማ እንዳለዉ ተገለጸ

2451

ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከጾታዊ ጥቃት ነጻ የሆነ ማህበረሰብ የመገንባት ዓላማ ያለው መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ገለጹ፡፡

«ጾታን መሰረት አድርገዉ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ከመከላከል አንጻር የአመራሮች ሚና» በሚል ርዕስ ለፌደራል ፍርድ ቤቶች አመራሮችና ሰብሳቢ ዳኞች በቢሾፍቱ ከተማ አዱላላ ሪዞርትና ስፓ ታሕሳስ 25 ቀን 2015 ዓ.ም የተዘጋጀ የስልጠና መርሐ-ግብር ተሒዷል፡፡

ለፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ሠራተኞች በንቃተ-ሕግ እንዲሁም ጾታን መሠረት ካደረገ ጉዳት ጋር በተያያዘ በሥነልቦናዊና በማሕበራዊ ድጋፎች እና መርሆዎች ላይ ሥልጠና ተሰጠ

2214

ከፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ሬጅስትራሮችና የአስተዳደር ሠራተኞች በንቃተ ሕግና የሴቶች ሰብዓዊ መብቶች በዓለም አቀፍና በኢትየጵያ ሕግ ላይ እንዲሁም ጾታን መሠረት ካደረገ ጉዳት ጋር በተያያዘ በሥነልቦናዊና ማሕበራዊ ድጋፎችና መርሆዎች ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች በአገራችን ላይ ስምምነቶቹን የማክበር፣ የማስከበር እና ሰብአዊ መብቶችን የማሟላት ግዴታ እንደሚጥሉባት ተጠቆመ

2630

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መቋቋሙን ተከትሎ የሰብዓዊ መብቶችን በሀገራት ለማስረጽና የሕግ ማዕቀፍ ለማበጀት የተለያዩ ሰብዓዊ መብት ስምምነቶችን በማርቀቅ በአባል አገራቱ እንዲጸድቅ ማድረጉንና ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች በአገራችን ላይ ስምምነቶቹን የማክበር፣ የማስከበር እና ሰብአዊ መብቶችን የማሟላት ግዴታ እንደሚጥሉባት ተጠቆመ፡፡

ጾታን መሠረት ባደረጉ የኃይል ጥቃቶች 90 በመቶ ያህል ጥቃት ፈጻሚዎች ሕጋዊ ቅጣት እንደማያገኙ ተመለከተ

2510

በአገራችን ጾታን መሠረት አድርገው ከሚፈጸሙ የኃይል ጥቃቶች መካከል 90 በመቶ ያህል ጥቃት ፈጻሚዎች ለፍትሕ ተቋማት ቀርበው ሕጋዊ ቅጣት እንደማያገኙ ተመለከተ፡፡

ጾታን መሰረት ያደረጉ የኃይል ጥቃቶች የወንጀል ምርመራ ቴክኒኮች፣ ፕሮቶኮል እንዲሁም አሠራሮችን በሚመለከት ለፌደራል ዳኞች እና ሌሎች የዳኝነት አካላት ሕዳር 17 እና 18 ቀን በአዳማ ከረዩ ሪዞርት ሆቴል ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት ከክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ጋር ያደረገዉን ቃለ ምልልስ ሕዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ እትሙ እንደሚከተለው አቅርቦታል

2570

Meaza Ashenafi, who is best recognized for her work to empower women, was elected as the Federal Supreme Court’s first female president. She has held this role ever since, leading numerous initiatives to modernize the justice system. It wasn’t an easy task, especially in a nation where the separation between the three branches of government—the Executive, the Legislature, and the Judiciary—is blurred.

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዚደንቶች፣ አመራሮችና ዳኞች ለክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ የእንኳን ደስ አለዎት መርሐ-ግብር አካሔዱ

2078

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የክርክር ፍርድ ቤት የግማሽ ጊዜ ዳኛ ሆነው መሾማቸውን ምክንያት በማድረግ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዚደንቶች፣ ዳኞችና የሥራ ኃላፊዎች ሕዳር 13 ቀን 2015 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ የእንኳን ደስ አለዎት መርሐ-ግብር አካሔዱ፡፡

First2829303133353637Last