ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተከበረ

401

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ፣ በአገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል የነገን ስብዕና ይገነባል" በሚል መሪ ቃል በመከበር ላይ የሚገኘው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ታህሳስ 4 ቀን 2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቱ ዳኞችና የአስተዳደር ሠራተኞች በተገኙበት ተከብሯል፡፡

በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ጋር ውይይት አደረጉ

186

በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ሶፊ ፍሮመስበርገር በቀን 02/04/2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ከፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል፡፡

በተባበሩት መንግስታት የህጻናት መብቶች ኮሚቴ አማካኝነት እየተዘጋጀ ባለው General Comment 27 on Access to Justice for children ላይ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ተካሄደ

378

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናትና ፍትህ ፕሮጀክት በተባበሩት መንግስታት የህጻናት መብቶች ኮሚቴ አማካኝነት እየተዘጋጀ ባለው General Comment 27 on Access to Justice for children የሃገራችን ህጻናት አስተያየት ለማካተት በማሰብ ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከአዲስ አበባ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች እና የህጻናት ፓርላማ የተውጣጡ ህጻናትን በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በማሰባሰብ ግብዓት ተቀብሏል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በአምስት የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የውይይትና ግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል

185

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች የሥልጠና ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት፣የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሥልጠና መመሪያ፣የእግድ አሰጣት እና አተገባበር ላይ፣በፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍትሕ መዘግየት ምክንያቶች እና ማነቆዎች በሚል በተዘጋጀ ሞጁል ላይ እንዲሁም የወሲባዊ ጥቃት ወንጀሎችን በተፋጠነ እና ተጎጅ ተኮር በሆነ መንገድ ለመዳኘት የሚያግዝ ማኑዋል ላይ ለሁለት ቀናት የቆየ የውይይትና ግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል፡፡  

በሸሪዓ ፍርድ ቤቶች የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በተዘጋጀ ረቂቅ የጥናት ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ

237

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የፌደራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት በጋራ በመሆን በሸሪዓ ፍርድ ቤቶች የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ባዘጋጁት ረቂቅ የጥናት ሰነድ ላይ በቀን 22/03/2017 ዓ.ም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡   

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ተገልጋዮች ለፍ/ቤት የሚቀርቡ መዛግብትን ባሉበት አካባቢ ሆነው ማስከፈት የሚችሉበት (e-filing) ሶፍትዌር እና የዳኞች መዝገብ መከታተያ ( judge’s Dashboard) ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ

230

በፍርድ ቤቱ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ ስርአት ተቋሙ እያከናቸው ከሚገኘው መጠነ ሰፊ የዲጅታላይዜሽን ስራዎች መካከል አንዱ ሲሆን የተገልጋዮችን እንግልት እና ወጪ የሚቀንስ፣ ግልፅና ተጠያቂነት ያለው አሰራር የሚያሰፍኑ እና ለዳኞች ምቹ የስራ ሁኔታን የሚፈጥሩ ናቸው::

124678910Last