በዳኝነት ሥርዓቱ በሚታዩ ችግሮችና ሊወሰዱ በሚገባቸው የመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተካሔደ

100

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት እና ም/ፕሬዚደንት በዳኝነት ሥርዓቱ ዙሪያ በሚታዩ ችግሮችና ሊወሰዱ በሚገባቸው የመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ ከሶስቱም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከተውጣጡ 150 ከሚሆኑ የፍ/ቤቶቹ አመራሮችና ዳኞች ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡

በዳኝነት ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከተለመደው አሠራር ወጣ ያሉ አዳዲስ አሠራሮችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቆመ

96

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አዲሱ አመራር በፍ/ቤቱ ሥራ የጀመረው የነበረውን አሠራር ለማስቀጠል ብቻ ሳይሆን በዳኝነት ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከተለመደው አሠራር ወጣ ያሉ አዳዲስ አሠራሮችን ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን የፍ/ቤቱ ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምሕረት ገለጹ፡፡

በፍርድ ቤቱ አዲስ ተሿሚ ፕሬዚደንቶች እና በቀድሞ ፕሬዚደንቶች መካከል የሥራ ርክክብ ሥነሥርዓት ተፈጸመ

82

 ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት አዲስ በተሾሙ ፕሬዚደንቶች እና በቀድሞ ፕሬዚደንቶች መካከል የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ በተገኙበት በፍርድ ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም በተካሔደ ሥነሥርዓት የሥራ ርክክብ ተካሔደ፡፡

"ፍርድ ቤቱ አገልግሎት ፈላጊዎችን በተሻለ ለማስተናገድ የሚረዱ ስራዎች ላይ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል"-የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

67

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አገልግሎት ፈላጊዎችን በተሻለ መልኩ ለማስተናገድ የሚረዱ የለውጥ ስራዎች ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳሰበ።

በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሕጎችና አዋጆች ሲወጡ ልዩ ትኩረት የሚፈልጉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ

57

አገራችን በርካታ ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶችን የተቀበለች እና በርካታ የሕግ ድንጋጌዎች ያሏት በመሆኑ ሕጎቹን ትኩረት የሚፈልጉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ማስተካከል፣ ወደፊት የሚወጡ ሕጎችንና አዋጆችን ደግሞ ይህን ታሳቢ ባደረገ ሁኔታ ማየት እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሕግ፣ ዲሞክራሲና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ዕፀገነት መንግሥቱ አስገነዘቡ፡፡

በፌደራል ፍ/ቤቶች የአምስት ዓመት ስትራትጅክ ዕቅድ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ አንድ ግብ የተቀመጠ መሆኑ ተገለጸ

69

በፌደራል ፍርድ ቤቶች ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ተግባራዊ እየተደረገ በሚገኘው ስትራቴጅክ ዕቅድ ላይ ከተቀመጡ ስድስት ቁልፍ የውጤት መስኮች አንዱ ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት መሆኑንና በዚህ ውስጥ የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደግብ ተይዞ በዚህ ዙሪያ የተለያዩ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደት ክብርት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ገለጹ፡፡

ፍርድ ቤቱ ከጾታዊ ጥቃት ነጻ የሆነ ማህበረሰብ የመገንባት ዓላማ እንዳለዉ ተገለጸ

75

ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከጾታዊ ጥቃት ነጻ የሆነ ማህበረሰብ የመገንባት ዓላማ ያለው መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ገለጹ፡፡

«ጾታን መሰረት አድርገዉ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ከመከላከል አንጻር የአመራሮች ሚና» በሚል ርዕስ ለፌደራል ፍርድ ቤቶች አመራሮችና ሰብሳቢ ዳኞች በቢሾፍቱ ከተማ አዱላላ ሪዞርትና ስፓ ታሕሳስ 25 ቀን 2015 ዓ.ም የተዘጋጀ የስልጠና መርሐ-ግብር ተሒዷል፡፡

ለፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ሠራተኞች በንቃተ-ሕግ እንዲሁም ጾታን መሠረት ካደረገ ጉዳት ጋር በተያያዘ በሥነልቦናዊና በማሕበራዊ ድጋፎች እና መርሆዎች ላይ ሥልጠና ተሰጠ

90

ከፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ሬጅስትራሮችና የአስተዳደር ሠራተኞች በንቃተ ሕግና የሴቶች ሰብዓዊ መብቶች በዓለም አቀፍና በኢትየጵያ ሕግ ላይ እንዲሁም ጾታን መሠረት ካደረገ ጉዳት ጋር በተያያዘ በሥነልቦናዊና ማሕበራዊ ድጋፎችና መርሆዎች ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

124678910Last