የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳኞችና የስራ ኃላፊዎች የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ

352

እንደ ሀገር የሚካሄደዉን የአየር ንብረት ለዉጥ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት የሚሰሩ ስራዎች አካል የሆነዉን እና ለ7ኛ ዙር እየተካሄደ ያለዉን ሀገር አቀፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ተጠሪ ተቋማት ተሳትፎ አድርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ለፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት አቀረበ

323

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ለፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በቀን 02/11/2017 ዓ.ም አቅርቧል፡፡

የዳሰሳ ጥናቱ ዓላማ በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የእውቀት፣ ክህሎት እና ሙያዊ አመለካከት ክፍተቶች ካሉ በዳሰሳ ጥናት በመለየት ለዳኞች የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ለመስጠት እና የዳኞችን የስልጠና ፍላጎት ለመለየት ነው፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር ዉይይት አደረገ

364

በዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡ የሚስተዋሉ ክፍተቶችና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም መፍትሄዎች ማስቀመጥ የሚቻልባቸዉ ሁኔታዎች ላይ የሚመክር የዉይይት መድረክ ሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡

የፌደራል ሸሪዓ ፍርድ ቤት አዋጅ ማሻሻያ እና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሄደ

429

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የፌደራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት በጋራ በመሆን የፌዴራል የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 188/92 እንዲሻሻል የጥናት ሰነድ እና የአዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ አዘጋጅ ቡድን ላደረጉት የስራ ትጋትና አስተዋጽኦ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም የምስጋና መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡

በወንጀል ነክ ድርጊት ዉስጥ ገብተዉ ከተገኙ ህጻናት እንዲሁም በሴቶች እና ህጻናት ችሎት ለሚሰሩ የፌዴራል ዳኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

768

በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በወንጀል ነክ ድርጊት ዉስጥ ገብተዉ ከተገኙ ህጻናት እንዲሁም በሴቶች እና ህጻናት ችሎት ለሚሰሩ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰኔ 14 እና 15 ቀን 2017 ዓ.ም ተሰጥቷል፡፡

የኢ-ፋይሊንግ እና የፕላዝማ ችሎት የስራ ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ

548

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ጋር በመተባበር በገላን ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ቤት ማዕከል ያሰራውን የኢ-ፋይሊንግ እና የፕላዝማ ችሎት ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ስራ አስጀምሯል፡፡

ፍርድ ቤቱ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ

541

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር የሁለቱን ተቋማት የትብብር መስክ ያጠናክራል የተባለ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ልዑካን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጉብኝት አደረጉ

559

የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ልዑካን ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።

123578910Last