የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አርባ ምንጭ ማዕከል የህንፃ እድሳት ምርቃት መርሃግብር ተካሄደ

694

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አርባ ምንጭ ማዕከል የህንፃ እድሳት ተደርጎ በሐምሌ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቋል።

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የእውቅና ሽልማት አበረከተ

653

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላደረገው አስተዋጽኦ፣ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኢንፎርሜሽንና ኮሚዩኒኬሽን ክፍል ሃላፊና ባለሙያዎች ላደረጉት ድጋፍ የእውቅና ምስክር ወረቀት አበርክቷል፡፡

በተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 ላይ ለፌደራልና ለክልል የፍትሕ ተቋማት ተሳታፊዎች ሲሰጥ የቆየው የአሰልጣኞች ሥልጠና ተጠናቀቀ

940

በአገራችን ፍርድ ቤቶች የቅጣት ውሳኔዎችን ወጥነት እና ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የቅጣት አወሳሰን መመሪያ መኖር አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህንኑ መመሪያ የማውጣት ሥልጣን በወንጀል ሕግ አንቀጽ 88(4) በተሰጠው መሠረት ፍርድ ቤቱ በቅርቡ አሻሽሎ ባወጣው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 ላይ ለፌደራልና ለክልል የፍትሕ ተቋማት ተሳታፊዎች ከሐምሌ 10-12 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሰጥ የቆየው የአሰልጣኞች ሥልጠና ተጠናቀቀ፡፡

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ወንጀል ችሎት ምድብ የሬጅስትራር አንድ መስኮት አገልግሎት ተመረቀ

926

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ወንጀል ችሎት ምድብ የሬጅስትራር አንድ መስኮት አገልግሎት ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት በክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት በክብርት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ ተመርቆ በይፋ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

የተዘዋዋሪ እና ቋሚ ምድብ ችሎቶች ክትትል እና ግምገማን ዓላማ ያደረገ ጉብኝት ተካሔደ

582

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚደንት በክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ የተመራ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አመራሮች ልዑክ በሶማሌ እና በሐረሪ ክልሎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች እንዲሁም በድሬዳዋ ምድብ ችሎቶች እና የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች በመዘዋወር የክትትል እና ግምገማ ጉብኝት አካሄደዋል፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳኞችና የስራ ኃላፊዎች የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ

646

እንደ ሀገር የሚካሄደዉን የአየር ንብረት ለዉጥ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት የሚሰሩ ስራዎች አካል የሆነዉን እና ለ7ኛ ዙር እየተካሄደ ያለዉን ሀገር አቀፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ተጠሪ ተቋማት ተሳትፎ አድርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ለፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት አቀረበ

753

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ለፌደራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በቀን 02/11/2017 ዓ.ም አቅርቧል፡፡

የዳሰሳ ጥናቱ ዓላማ በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የእውቀት፣ ክህሎት እና ሙያዊ አመለካከት ክፍተቶች ካሉ በዳሰሳ ጥናት በመለየት ለዳኞች የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ለመስጠት እና የዳኞችን የስልጠና ፍላጎት ለመለየት ነው፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር ዉይይት አደረገ

710

በዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡ የሚስተዋሉ ክፍተቶችና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም መፍትሄዎች ማስቀመጥ የሚቻልባቸዉ ሁኔታዎች ላይ የሚመክር የዉይይት መድረክ ሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡

123468910Last