የፌደራል ፍርድ ቤቶች የዋይድ ኤርያ ኔትወርክ ፕሮጀክት አፈጻጸም ያለበት ደረጃ ክትትልና ግምገማ ተካሄደ

619

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በዋይድ ኤርያ ኔትወርክ (WAN) ለማገናኘት እየተከናወነ የሚገኘውን የፕሮጀክት አፈጻጸም የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሕግ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የፕላንና በጀት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ የኢትዮ ቴሌኮም የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃና ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንዲሁም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡

በተከታታይ የወንጀል ክስ አሰማም ሂደት ዙሪያ በተዘጋጀ ጥናት ላይ የማረጋገጫ እና የውይይት መድረክ (Validation and Consultation Workshop) ተካሔደ

2014

ከፌደራል ፍርድ ቤቶች፣ ከፍትሕ ሚኒስቴር፣ ከፌደራልና ከአዲስ አበባ ፖሊስ፣ ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር እና ከፌደራል ጠበቆች ማሕበር የተወከሉ የሥራ ኃላፊዎች፣ ዳኞች እንዲሁም ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በተከታታይ የወንጀል ክስ አሰማም ሂደት (Continuous Criminal Trial) ላይ ‹‹Assessment of gaps that obstruct continuous ctriminal trials in federal courts›› በሚል ርዕስ በተከናወነ ጥናት ላይ የማረጋገጫ እና የምክክር መድረክ (Validation Workshop) ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሄዷል፡፡

ፍርድ ቤቱ የሰበር ዉሳኔ የድምጽ ቅጂ ለኢትዮጵያ ዓይነ ስዉራን ብሔራዊ ማህበር አበረከተ

750

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስገዳጅ የህግ ትርጉም የሰጠባቸዉን በድምጽ ቅጂ መልክ የተዘጋጁ ከቅጽ 1-18 ያሉ የሰበር ዉሳኔዎች ለኢትዮጵያ ዓይነ ስዉራን ብሄራዊ ማህበር ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ/ም አበረከተ።

ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና የስራ ሃላፊዎች የ‹‹stress management›› & ‹‹ emotional intelligence›› በሚል ርዕሰ ጉዳይ የክህሎት ስልጠና ተሰጠ

718

ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና የስራ ሃላፊዎች በቀን 22/10/2016 ዓ.ም ‹‹stress management›› & ‹‹ emotional intelligence›› በሚል ርዕሰ ጉዳይ የክህሎት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ የስልጠናው አላማ ዳኞችና የፍርድ ቤት የስራ ሃላፊዎች ከዕለት ተዕለት ስራቸው ጋር በተገናኘ ጫናዎችን የሚያስተናግዱበት፣ የሚቋቋሙበትንና የአመራር ክህሎትን የሚያሳድጉባቸው ክህሎቶች/ዘዴዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨባጫ መስጠት ነው።

በሩሲያ ፌዴሬሽን የሕገመንግስት ፍርድ ቤት በተዘጋጀውና ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ25 በላይ ሃገራት ህገመንግስታዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንቶች በተገኙበት ‹‹Protection of Rights and Constitutional Supervision›› በሚል ርዕስ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ተካሂዷል

628

በሩሲያ ፌዴሬሽን የሕገመንግስት ፍርድ ቤት ‹‹Protection of Rights and Constitutional Supervision›› በሚል ርዕስ በቀን 19/10/2016 ዓ.ም በተዘጋጀውና ከ25 በላይ ሃገራት ህገመንግስታዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንቶች በተገኙበት ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ላይ የኢፌዲሪ የሕገመንግሥት አጣሪ ጉባኤ ሰብሳቢና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በሩሲያ ፌዴሬሽን በሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ሕገመንግሥታዊ ፍርድ ቤት በመገኘት የኢፌድሪ የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤን ሚና፣ አወቃቀር፣ አደረጃጀትና አሠራር፣ ሥልጣንና ተግባራቱን በተመለከተ ያለውን ተሞክሮ አቅርበዋል

በህጻናት ዝቅተኛ የወንጀል ተጠያቂነት እድሜ ላይ ያተኮረ ስልጠና እና ውይይት ከኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጋር ተካሄደ

772

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት እና በUNFPA ትብብር የህጻናት የወንጀል ተጠያቂነት ዝቅተኛ እድሜን በተመለከተ ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ከክቡራን የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ውይይት ተደርጓል

የፍርድ ቤቱ የፍትሃብሄር ይግባኝ ሰሚ ችሎት ሰራተኞች እና ሀላፊዎች ጋር የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ውይይት አደረጉ

596

 የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የፍትሃብሄር ይግባኝ ሰሚ ችሎት ሰራተኞች ከሀላፊዎች ጋር በመሆን የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ.ም ውይይት አድርገዋል

የብሪክስ አባል ሃገራት የጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶች ፎረም ተጠናቀቀ

695

በራሽያ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ከሰኔ 10-14 ቀን 2016 ዓ/ም ሲካሄድ የቆየው የብሪክስ አባል ሀገራት ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶች ለ5 ቀናት የተሳተፉበትና “ብሪክስ ቺፍ ጀስቲስ ፎረም” በሚል ርዕስ ሲካሄድ የነበረዉ የጋራ የዉይይት መድረከ ተጠናቀቀ

First34568101112Last